ኦሪት ዘፍጥረት Orit ZeFiTret
Genesis / Bereisheit #22
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘፍጥረት 22

Genesis 22

1 ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው፥ እንዲህም አለው፦ አብርሃም ሆይ፦ አብርሃምም፦ እነሆ፥ አለሁ አለ።

1 And it came to pass after these things, that God did tempt Abraham, and said unto him, Abraham: and he said, Behold, here I am.

2 የምትወደውን አንድ ልጅህን ይስሐቅን ይዘህ ወደ ሞሪያም ምድር ሂድ እኔም በምነግርህ በአንድ ተራራ ላይ በዚያ መሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ።

2 And he said, Take now thy son, thine only son Isaac, whom thou lovest, and get thee into the land of Moriah; and offer him there for a burnt offering upon one of the mountains which I will tell thee of.

3 አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፥ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሕቅን ከእርሱ ጋር ወሰደ፥ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነሥቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።

3 And Abraham rose up early in the morning, and saddled his ass, and took two of his young men with him, and Isaac his son, and clave the wood for the burnt offering, and rose up, and went unto the place of which God had told him.

4 በሦስተኛውም ቀን አብርሃም ዓይኑን አነሣና ቦታውን ከሩቅ አየ።

4 Then on the third day Abraham lifted up his eyes, and saw the place afar off.

5 አብርሃምም ሎሌዎቹን አላቸው፦ አህያውን ይዛችሁ ከዚህ ቆዩ እኔና ልጄ ወደዚያ ሄደን እንሰግዳለን፥ ወደ እናንተም እንመለሳለን።

5 And Abraham said unto his young men, Abide ye here with the ass; and I and the lad will go yonder and worship, and come again to you.

6 አብርሃምም የመሥዋዕቱን እንጨት አንሥቶ ለልጁ ለይስሐቅ አሸከመው እርሱም እሳቱንና ቢላዋውን በእጁ ያዘ፥ ሁለቱም አብረው ሄዱ።

6 And Abraham took the wood of the burnt offering, and laid it upon Isaac his son; and he took the fire in his hand, and a knife; and they went both of them together.

7 ይስሐቅም አባቱን አብርሃምን ተናገረው፦ አባቴ ሆይ አለ። እርሱም፦ እነሆኝ፥ ልጄ አለው። እሳቱና እንጨቱ ይኸው አለ የመሥዋዕቱ በግ ግን ወዴት ነው? አለ።

7 And Isaac spake unto Abraham his father, and said, My father: and he said, Here am I, my son. And he said, Behold the fire and the wood: but where is the lamb for a burnt offering?

8 አብርሃምም፦ ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው ሁለቱም አብረው ሄዱ።

8 And Abraham said, My son, God will provide himself a lamb for a burnt offering: so they went both of them together.

9 እግዚአብሔር ወዳለውም ቦታ ደረሱ አብርሃምም በዚያ መሠዊያውን ሠራ፥ እንጨትንም ረበረበ ልጁን ይስሐቅንም አስሮ በመሠዊያው በእንጨቱ ላይ አጋደመው።

9 And they came to the place which God had told him of; and Abraham built an altar there, and laid the wood in order, and bound Isaac his son, and laid him on the altar upon the wood.

10 አብርሃምም እጁን ዘረጋ፥ ልጁንም ያርድ ዘንድ ቢላዋ አነሣ።

10 And Abraham stretched forth his hand, and took the knife to slay his son.

11 የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። አብርሃም አብርሃም አለው

11 And the angel of the Lord called unto him out of heaven, and said, Abraham, Abraham: and he said, Here am I.

12 እርሱም፦ እነሆኝ አለ። እርሱም፦ በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፥ አንዳችም አታድርግበት አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደ ሆንህ አሁን አውቄአለሁ አለ።

12 And he said, Lay not thine hand upon the lad, neither do thou any thing unto him: for now I know that thou fearest God, seeing thou hast not withheld thy son, thine only son from me.

13 አብርሃምም ዓይኑን አነሣ፥ በኋላውም እነሆ አንድ በግ በዱር ውስጥ ቀንዶቹ በዕፀ ሳቤቅ ተይዞ አየ አብርሃምም ሄደ በጉንም ወሰደው፥ በልጁም ፋንታ መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው።

13 And Abraham lifted up his eyes, and looked, and behold behind him a ram caught in a thicket by his horns: and Abraham went and took the ram, and offered him up for a burnt offering in the stead of his son.

14 አብርሃምም ያንን ቦታ ያህዌ ይርኤ ብሎ ጠራው እስከ ዛሬም ድረስ በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል ይባላል።

14 And Abraham called the name of that place Jehovah–jireh: as it is said to this day, In the mount of the Lord it shall be seen.

15 የእግዚአብሔር መልአክም አብርሃምን ከሰማይ ሁለተኛ ጊዜ ጠራው፥

15 And the angel of the Lord called unto Abraham out of heaven the second time,

16 እንዲህም አለው፦ እግዚአብሔር፦ በራሴ ማልሁ ይላል ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና

16 And said, By myself have I sworn, saith the Lord, for because thou hast done this thing, and hast not withheld thy son, thine only son:

17 በእውነት በረከትን እባርክሃለሁ፥ ዘርህንም እንደ ሰማይ ከዋክብትና በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ አበዛዋለሁ ዘርህም የጠላቶችን ደጅ ይወርሳል

17 That in blessing I will bless thee, and in multiplying I will multiply thy seed as the stars of the heaven, and as the sand which is upon the sea shore; and thy seed shall possess the gate of his enemies;

18 የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፥ ቃሌን ሰምተሃልና።

18 And in thy seed shall all the nations of the earth be blessed; because thou hast obeyed my voice.

19 አብርሃምም ወደ ብላቴኖቹ ተመለሰ፥ ተነሥተውም ወደ ቤርሳቤህ አብረው ሄዱ አብርሃምም በቤርሳቤህ ተቀመጠ።

19 So Abraham returned unto his young men, and they rose up and went together to Beer–sheba; and Abraham dwelt at Beer–sheba.

20 ይህም ከሆነ በኋልላ ለአብርሃም እንዲህ ተብሎ ተነገረ። እነሆ፥ ሚልካ ደግሞ ለወንድምህ ለናኮር ልጆችን ወለደች

20 And it came to pass after these things, that it was told Abraham, saying, Behold, Milcah, she hath also born children unto thy brother Nahor;

21 እነርሱም በኵሩ ዑፅ፥ ወንድሙ ቡዝ፥ የአራም አባት ቀሙኤል፥

21 Huz his firstborn, and Buz his brother, and Kemuel the father of Aram,

22 ኮዛት፥ ሐዞ፥ ፊልዳሥ፥ የድላፍ፥ ባቱኤል ናቸው።

22 And Chesed, and Hazo, and Pildash, and Jidlaph, and Bethuel.

23 ባቱኤልም ርብቃን ወለደ እነዚህን ስምንቱን ሚልካ ለአብርሃም ወንድም ለናኮር ወለደች።

23 And Bethuel begat Rebekah: these eight Milcah did bear to Nahor, Abraham’s brother.

24 ሬሕማ የሚሉአት ቁባቱ ደግሞ ጥባህን፥ ገአምን፥ ተሐሸን፥ ሞክሳን ወለደች።

24 And his concubine, whose name was Reumah, she bare also Tebah, and Gaham, and Thahash, and Maachah.