መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #101
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 101

Psalm 101

1 አቤቱ፥ ምሕረትንና ፍርድን እቀኝልሃለሁ።

1 I will sing of mercy and judgment: unto thee, O Lord, will I sing.

2 እዘምራለሁ፥ ንጹሕ መንገዱንም አስተውላለሁ ወደ እኔ መቼ ትመጣለህ? በቤቴ መካከል በልቤ ቅንነት እሄዳለሁ።

2 I will behave myself wisely in a perfect way. O when wilt thou come unto me? I will walk within my house with a perfect heart.

3 በዓይኔ ፊት ክፉን ነገር አላኖርሁም ሕግ ተላላፊዎችን ጠላሁ።

3 I will set no wicked thing before mine eyes: I hate the work of them that turn aside; it shall not cleave to me.

4 ጠማማ ልብም አልተጠጋኝም ክፉ ከእኔ በራቀ ጊዜ አላወቅሁም።

4 A froward heart shall depart from me: I will not know a wicked person.

5 ባልንጀራውን በቀስታ የሚያማን እርሱን አሳደድሁ በዓይኑ ትዕቢተኛ የሆነውና ልቡ የሚሳሳው ከእኔ ጋር አይተባበርም።

5 Whoso privily slandereth his neighbour, him will I cut off: him that hath an high look and a proud heart will not I suffer.

6 ከእኔ ጋር ይኖሩ ዘንድ ዓይኖቼ በምድር ምእመናን ላይ ናቸው በቀና መንገድ የሚሄድ እርሱ ያገለግለኛል።

6 Mine eyes shall be upon the faithful of the land, that they may dwell with me: he that walketh in a perfect way, he shall serve me.

7 ትዕቢትን የሚያደርግ በቤቴ መካከል አይኖርም ዓመፅን የሚናገር በዓይኔ ፊት አይቀናም።

7 He that worketh deceit shall not dwell within my house: he that telleth lies shall not tarry in my sight.

8 ዓመፃ የሚያደርጉትን ሁሉ ከእግዚአብሔር ከተማ አጠፋቸው ዘንድ፥ የምድርን ኃጢአተኞች ሁሉ በማለዳ እገድላቸዋለሁ።

8 I will early destroy all the wicked of the land; that I may cut off all wicked doers from the city of the Lord.