ኦሪት ዘፍጥረት Orit ZeFiTret
Genesis / Bereisheit #46
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘፍጥረት 46

Genesis 46

1 እስራኤልም ለእርሱ ያለውን ሁሉ ይዞ ተነሣ፥ ወደ ቤርሳቤህ መጣ፥ መሥዋዕትንም ለአባቱ ለይስሐቅ አምላክ ሠዋ።

1 And Israel took his journey with all that he had, and came to Beer–sheba, and offered sacrifices unto the God of his father Isaac.

2 እግዚአብሔርም በሌሊት ራእይ። ያዕቆብ ያዕቆብ ብሎ ለእስራኤል ተናገረው። እርሱም፦ እነሆኝ አለ።

2 And God spake unto Israel in the visions of the night, and said, Jacob, Jacob. And he said, Here am I.

3 አለውም፦ የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ ወደ ግብፅ መውረድ አትፍራ፥ በዚያ ትልቅ ሕዝብ አደርግሃለሁና።

3 And he said, I am God, the God of thy father: fear not to go down into Egypt; for I will there make of thee a great nation:

4 እኔ ወደ ግብፅ አብሬህ እወርዳለሁ፥ ከዚያም ደግሞ እኔ አወጣሃለሁ ዮሴፍም እጁን በዓይንህ ላይ ያኖራል።

4 I will go down with thee into Egypt; and I will also surely bring thee up again: and Joseph shall put his hand upon thine eyes.

5 ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ተነሣ የእስራኤልም ልጆች ያዕቆብን ይወስዱ ዘንድ ፈርዖን በሰደዳቸው ሰረገሎች አባታቸውን ያዕቆብንና ሕፃናቶቻቸውን ሴቶቻቸውንም ወሰዱ።

5 And Jacob rose up from Beer–sheba: and the sons of Israel carried Jacob their father, and their little ones, and their wives, in the wagons which Pharaoh had sent to carry him.

6 እንስሶቻቸውንም በከነዓን አገርም ያገኙትን ከብታቸውን ሁሉ ይዘው ያዕቆብና ዘሩ ሁሉ ከእርሱ ጋር ወደ ግብፅ መጡ

6 And they took their cattle, and their goods, which they had gotten in the land of Canaan, and came into Egypt, Jacob, and all his seed with him:

7 ወንዶች ልጆቹንና የልጆቹን ወንዶች ልጆች፥ ሴቶች ልጆቹንና የወንዶች ልጆቹን ሴቶች ልጆች፥ ዘሩንም ሁሉ ከእርሱ ጋር ወደ ግብፅ አስገባቸው።

7 His sons, and his sons’ sons with him, his daughters, and his sons’ daughters, and all his seed brought he with him into Egypt.

8 ወደ ግብፅም የገቡት የእስራኤል ልጆች ስም ይህ ነው፥ ያዕቆብና ልጆቹ የያዕቆብ በኵር ሮቤል።

8 And these are the names of the children of Israel, which came into Egypt, Jacob and his sons: Reuben, Jacob’s firstborn.

9 የሮቤልም ልጆች ሄኖኅ፥ ፈሉሶ፥ አስሮን፥ ከርሚ።

9 And the sons of Reuben; Hanoch, and Phallu, and Hezron, and Carmi.

10 የስሞዖን ልጆች ይሙኤል፥ ያሚን፥ ኦሃድ፥ ያኪን፥ ጾሐር፥ የከነዓናዊት ልጅ ሳኡል።

10 And the sons of Simeon; Jemuel, and Jamin, and Ohad, and Jachin, and Zohar, and Shaul the son of a Canaanitish woman.

11 የሌዊም ልጆች ጌድሶን፥ ቀዓት፥ ሜራሪ።

11 And the sons of Levi; Gershon, Kohath, and Merari.

12 የይሁዳም ልጆች ዔር፥ አውናን፥ ሴሎም፥ ፋሬስ፥ ዛራ ዔርና አውናን በከነዓን ምድር ሞቱ የፋሬስም ልጆች ኤስሮም፥ ሐሙል።

12 And the sons of Judah; Er, and Onan, and Shelah, and Pharez, and Zerah: but Er and Onan died in the land of Canaan. And the sons of Pharez were Hezron and Hamul.

13 የይሳኮርም ልጆች ቶላ፥ ፉዋ፥ ዮብ፥ ሺምሮን።

13 And the sons of Issachar; Tola, and Phuvah, and Job, and Shimron.

14 የዛብሎንም ልጆች ሴሬድ፥ ኤሎን፥ ያሕልኤል።

14 And the sons of Zebulun; Sered, and Elon, and Jahleel.

15 ልያ በመስጴጦምያ በሶርያ ለያዕቆብ የወለደቻቸው ልጆችና ሴቲቱ ልጅዋ ዲና እነዚህ ናቸው ወንዶችም ሴቶችም ልጆችዋ ሁሉ ሠላሳ ሦስት ነፍስ ናቸው።

15 These be the sons of Leah, which she bare unto Jacob in Padan–aram, with his daughter Dinah: all the souls of his sons and his daughters were thirty and three.

16 የጋድም ልጆች ጽፎን፥ ሐጊ፥ ሹኒ፥ ኤስቦን፥ ዔሪ፥ አሮዲ፥ አርኤሊ።

16 And the sons of Gad; Ziphion, and Haggi, Shuni, and Ezbon, Eri, and Arodi, and Areli.

17 የአሴርም ልጆች ዪምና፥ የሱዋ፥ የሱዊ፥ በሪዓ፥ እኅታቸው ሤራሕ የበሪዓ ልጆችም ሔቤር፥ መልኪኤል።

17 And the sons of Asher; Jimnah, and Ishuah, and Isui, and Beriah, and Serah their sister: and the sons of Beriah; Heber, and Malchiel.

18 ላባ ለልጁ ለልያ የሰጣት የዘለፋ ልጆች እነዚህ ናቸው እነዚህን አሥራ ስድስቱንም ነፍስ ለያዕቆብ ወለደች።

18 These are the sons of Zilpah, whom Laban gave to Leah his daughter, and these she bare unto Jacob, even sixteen souls.

19 የያዕቆብ ሚስት የራሔል ልጆች ዮሴፍና ብንያም ናቸው።

19 The sons of Rachel Jacob’s wife; Joseph, and Benjamin.

20 ለዮሴፍም በግብፅ ምድር ምናሴና ኤፍሬም ተወለዱለት የሄልዮቱ ከተማ ካህን የጶጥፌራ ልጅ አስናት የወለደቻቸው ናቸው።

20 And unto Joseph in the land of Egypt were born Manasseh and Ephraim, which Asenath the daughter of Poti–pherah priest of On bare unto him.

21 የብንያምም ልጆች ቤላ፥ ቤኬር፥ አስቤል የቤላ ልጆችም ጌራ፥ ናዕማን፥ አኪ፥ ሮስ፥ ማንፌን፥ ሑፊም ጌራም አርድን ወለደ።

21 And the sons of Benjamin were Belah, and Becher, and Ashbel, Gera, and Naaman, Ehi, and Rosh, Muppim, and Huppim, and Ard.

22 ለያዕቆብ የተወለዱለት የራሔልም ልጆች እነዚህ ናቸው ሁሉም አሥራ አራት ነፍስ ናቸው።

22 These are the sons of Rachel, which were born to Jacob: all the souls were fourteen.

23 የዳንም ልጆች ሑሺም።

23 And the sons of Dan; Hushim.

24 የንፍታሌምም ልጆች ያሕጽኤል፥ ጉኒ፥ ዬጽር፥ ሺሌም።

24 And the sons of Naphtali; Jahzeel, and Guni, and Jezer, and Shillem.

25 ላባ ለልጁ ለራሔል የሰጣት የባላ ልጆች እነዚህ ናቸው እነዚህንም ለያዕቆብ ወለደችለት ሁሉም ሰባት ነፍስ ናቸው።

25 These are the sons of Bilhah, which Laban gave unto Rachel his daughter, and she bare these unto Jacob: all the souls were seven.

26 ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ የገቡት ሰዎች ሁሉ ከጉልበቱ የወጡት፥ ከልጆቹ ሚስቶች ሌላ፥ ሁላቸው ስድሳ ስድስት ናቸው።

26 All the souls that came with Jacob into Egypt, which came out of his loins, besides Jacob’s sons’ wives, all the souls were threescore and six;

27 በግብፅ ምድር የተወለዱለት የዮሴፍም ልጆች ሁለት ናቸው ወደ ግብፅ የገቡት የያዕቆብ ቤተ ሰዎች ሁሉ ሰባ ናቸው።

27 And the sons of Joseph, which were born him in Egypt, were two souls: all the souls of the house of Jacob, which came into Egypt, were threescore and ten.

28 ይሁዳንም በጌሤም እንዲቀበለው በፊቱ ወደ ዮሴፍ ላከ ወደ ጌሤም ምድርም ደረሱ።

28 And he sent Judah before him unto Joseph, to direct his face unto Goshen; and they came into the land of Goshen.

29 ዮሴፍም ሰረገላውን አዘጋጀ፥ አባቱንም እስራኤልን ሊገናኘው ወደ ጌሤም ወጣ ባየውም ጊዜ በአንገቱ ላይ ወደቀ፥ አቅፎትም ረጅም ጊዜ አለቀሰ።

29 And Joseph made ready his chariot, and went up to meet Israel his father, to Goshen, and presented himself unto him; and he fell on his neck, and wept on his neck a good while.

30 እስራኤልም ዮሴፍን፦ አንተ ገና በሕይወት ሳለህ ፊትህን አይቼአለሁና አሁን ልሙት አለው።

30 And Israel said unto Joseph, Now let me die, since I have seen thy face, because thou art yet alive.

31 ዮሴፍም ወንድሞቹንና የአባቱን ቤተ ሰዎች እንዲህ አላቸው፦ እኔ መጥቼ ለፈርዖን እንዲህ ብዬ እነግረዋለሁ። በከነዓን ምድር የነበሩት ወንድሞቼና የአባቴ ቤተ ሰዎች ወደ እኔ መጥተዋል

31 And Joseph said unto his brethren, and unto his father’s house, I will go up, and shew Pharaoh, and say unto him, My brethren, and my father’s house, which were in the land of Canaan, are come unto me;

32 እነርሱም በግ የሚጠብቁ ሰዎች ናቸው፥ እንስሳ ያረቡ ነበርና በጎቻቸውንና ላሞቻቸውን ያላቸውንም ሁሉ አመጡ።

32 And the men are shepherds, for their trade hath been to feed cattle; and they have brought their flocks, and their herds, and all that they have.

33 ፈርዖንም ቢጠራችሁ። ተግባራችሁስ ምንድር ነው? ቢላችሁ፥

33 And it shall come to pass, when Pharaoh shall call you, and shall say, What is your occupation?

34 በግ ጠባቂ ሁሉ ለግብፅ ሰዎች ርኵስ ነውና በጌሤም እንድትቀመጡ እንዲህ በሉት። እኛ ባሪያዎችህ ከብላቴናነታችን ጀምረን እስከ አሁን ድረስ፥ እኛም አባቶቻችንም፥ እንስሳ አርቢዎች ነን።

34 That ye shall say, Thy servants’ trade hath been about cattle from our youth even until now, both we, and also our fathers: that ye may dwell in the land of Goshen; for every shepherd is an abomination unto the Egyptians.