ኦሪት ዘፍጥረት Orit ZeFiTret
Genesis / Bereisheit #24
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘፍጥረት 24

Genesis 24

1 አብርሃምም ሸመገለ በዘመኑም አረጀ እግዚአብሔርም አብርሃምን በሥራው ሁሉ ባረከው።

1 And Abraham was old, and well stricken in age: and the Lord had blessed Abraham in all things.

2 አብርሃምም ሎሌውን የቤቱን ሽማግሌ የከብቱን ሁሉ አዛዥ አለው።

2 And Abraham said unto his eldest servant of his house, that ruled over all that he had, Put, I pray thee, thy hand under my thigh:

3 እጅህን ከጭኔ በታች አድርግ፥ እኔም አብሬ ከምኖራቸው ከከነዓን ሴቶች ልጆች ለልጄ ሚስት እንዳትወስድለት በሰማይና በምድር አምላክ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ

3 And I will make thee swear by the Lord, the God of heaven, and the God of the earth, that thou shalt not take a wife unto my son of the daughters of the Canaanites, among whom I dwell:

4 ነገር ግን ወደ አገሬና ወደ ተወላጆቼ ትሄዳለህ፥ ለልጄ ለይስሐቅም ሚስትን ትወስድለታለህ።

4 But thou shalt go unto my country, and to my kindred, and take a wife unto my son Isaac.

5 ሎሌውም፦ ሴቲቱ ምናልባት ወደዚህ አገር ከእኔ ጋር ለመምጣት እንቢ ያለች እንደ ሆነ ልጅህን ወደ ወጣህበት አገር ልመልሰውን? አለው።

5 And the servant said unto him, Peradventure the woman will not be willing to follow me unto this land: must I needs bring thy son again unto the land from whence thou camest?

6 አብርሃምም አለው። ልጄን ወደዚያ እንዳትመልስ ተጠንቀቅ

6 And Abraham said unto him, Beware thou that thou bring not my son thither again.

7 ከአባቴ ቤት ከተወለድሁባት ምድርም ያወጣኝ፦ ይህችንም ምድር እሰጥሃለሁ ብሎ የነገረኝና የማለልኝ የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር፥ እርሱ መልአኩን በፊትህ ይሰድዳል፥ ከዚያም ለልጄ ሚስትን ትወስዳለህ።

7 The Lord God of heaven, which took me from my father’s house, and from the land of my kindred, and which spake unto me, and that sware unto me, saying, Unto thy seed will I give this land; he shall send his angel before thee, and thou shalt take a wife unto my son from thence.

8 ሴቲቱም ከአንተ ጋር ለመምጣት እንቢ ያለች እንደ ሆነ ከዚህ ካቀረብሁህ መሐላ ንጹሕ ነህ ልጄን ግን ወደዚያ አትመልሰው።

8 And if the woman will not be willing to follow thee, then thou shalt be clear from this my oath: only bring not my son thither again.

9 ሎሌውም ከጌታው ከአብርሃም ጭን በታች እጁን አደረገ ስለዚሁም ነገር ማለለት።

9 And the servant put his hand under the thigh of Abraham his master, and sware to him concerning that matter.

10 ሎሌውም ከጌታው ግመሎች መካከል አሥር ግመሎችን ወስዶ፥ ከጌታውም ዕቃ መልካም መልካሙን ይዞ ተነሣ ተነሥቶም ወደ መስጴጦምያ ወደ ናኮር ከተማ ሄደ።

10 And the servant took ten camels of the camels of his master, and departed; for all the goods of his master were in his hand: and he arose, and went to Mesopotamia, unto the city of Nahor.

11 ሲመሽም ሴቶች ውኃ ሊቀዱ በሚወጡበት ጊዜ ከከተማይቱ ውጪ በውኃው ጕድጓድ አጠገብ ግመሎቹን አስበረከከ።

11 And he made his camels to kneel down without the city by a well of water at the time of the evening, even the time that women go out to draw water.

12 እንዲህም አለ፦ የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ እለምንሃለሁ መንገዴን ዛሬ በፊቴ አቅናልኝ፥ ለጌታዬም ለአብርሃም ምሕረትን አድርግ።

12 And he said, O Lord God of my master Abraham, I pray thee, send me good speed this day, and shew kindness unto my master Abraham.

13 እነሆ፥ በዚህ የውኃ ምንጭ አጠገብ እኔ ቆሜአለሁ፥ የዚህችም ከተማ ሴቶች ልጆች ውኃውን ሊቀዱ ይመጣሉ

13 Behold, I stand here by the well of water; and the daughters of the men of the city come out to draw water:

14 ውኃ እጠጣ ዘንድ እንስራሽን አዘንብዪ የምላት እርስዋም፦ አንተ ጠጣ፥ ግመሎችህን ደግሞ አጠጣለሁ የምትለኝ ቆንጆ፥ እርስዋ ለባሪያህ ለይስሐቅ ያዘጋጀሃት ትሁን በዚህም ለጌታዬ ምሕረትን እንዳደረግህ አውቃለሁ።

14 And let it come to pass, that the damsel to whom I shall say, Let down thy pitcher, I pray thee, that I may drink; and she shall say, Drink, and I will give thy camels drink also: let the same be she that thou hast appointed for thy servant Isaac; and thereby shall I know that thou hast shewed kindness unto my master.

15 ይህን መናገሩንም ሳይፈጽም እነሆ፥ ሚልካ የወለደችው የባቱኤል ልጅ ርብቃ እንስራዋን በጫንቃዋ ተሸክማ ወጣች ሚልካም የአብርሃም ወንድም የናኮር ሚስት ናት።

15 And it came to pass, before he had done speaking, that, behold, Rebekah came out, who was born to Bethuel, son of Milcah, the wife of Nahor, Abraham’s brother, with her pitcher upon her shoulder.

16 ብላቴናይቱም መልክዋ እጅግ ያማረ፥ ወንድ የማያውቃት ድንግልም ነበረች ወደ ምንጭም ወረደች እንስራዋንም ሞላች፥ ተመልሳም ወጣች።

16 And the damsel was very fair to look upon, a virgin, neither had any man known her: and she went down to the well, and filled her pitcher, and came up.

17 ሎሌውም ሊገናኛት ሮጠና፦ ከእንስራሽ ጥቂት ውኃ ታጠጪኝ ዘንድ እለምንሻለሁ አላት።

17 And the servant ran to meet her, and said, Let me, I pray thee, drink a little water of thy pitcher.

18 እርስዋም፦ ጌታዬ ሆይ፥ ጠጣ አለችው ፈጥናም እንስራዋን በእጅዋ አውርዳ አጠጣችው።

18 And she said, Drink, my lord: and she hasted, and let down her pitcher upon her hand, and gave him drink.

19 እርሱንም ካጠጣች በኋላ፦ ለግመሎችህ ደግሞ ሁሉም እስኪረኩ ድረስ ውኃ እቀዳለሁ አለች።

19 And when she had done giving him drink, she said, I will draw water for thy camels also, until they have done drinking.

20 ፈጥናም ውኃውን ከእንስራዋ በማጠጫው ውስጥ ገለበጠችው፥ ደግሞም ልትቀዳ ወደ ጕድጓዱ ሮጠች፥ ለግመሎቹም ሁሉ ውኃ ቀዳች።

20 And she hasted, and emptied her pitcher into the trough, and ran again unto the well to draw water, and drew for all his camels.

21 ሰውዮውም ትክ ብሎ ይመለከታት ነበር እግዚአብሔር መንገዱን አቅንቶለት እንደ ሆነ ወይም እንዳልሆነ ለማወቅም ዝም አለ።

21 And the man wondering at her held his peace, to wit whether the Lord had made his journey prosperous or not.

22 ግመሎቹም ከጠጡ በኋላ እንዲህ ሆነ ሰውዮው ግማሽ ሰቅል የሚመዘን የወርቅ ቀለበት፥ ለእጆችዋም አሥር ሰቅል የሚመዘን ጥንድ የወርቅ አምባር አወጣ

22 And it came to pass, as the camels had done drinking, that the man took a golden earring of half a shekel weight, and two bracelets for her hands of ten shekels weight of gold;

23 እንዲህም አላት። አንቺ የማን ልጅ ነሽ? እስኪ ንገሪኝ በአባትሽ ቤት የምናድርበት ስፍራ ይገኛልን?

23 And said, Whose daughter art thou? tell me, I pray thee: is there room in thy father’s house for us to lodge in?

24 አለችውም፦ እኔ ሚልካ ለናኮር የወለደችው የባቱኤል ልጅ ነኝ።

24 And she said unto him, I am the daughter of Bethuel the son of Milcah, which she bare unto Nahor.

25 በእኛ ዘንድ ገለባና ገፈራ የሚበቃ ያህል አለ፥ ለማደሪያም ደግሞ ስፍራ አለን።

25 She said moreover unto him, We have both straw and provender enough, and room to lodge in.

26 ሰውዮውም አጎነበሰ፥ ለእግዚአብሔርም ሰገደ።

26 And the man bowed down his head, and worshipped the Lord.

27 እንዲህም አለ፦ ቸርነቱንና እውነቱን ከጌታዬ ያላራቀ የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን እኔ በመንገድ ሳለሁ እግዚአብሔር ወደ ጌታዬ ወንድሞች ቤት መራኝ።

27 And he said, Blessed be the Lord God of my master Abraham, who hath not left destitute my master of his mercy and his truth: I being in the way, the Lord led me to the house of my master’s brethren.

28 ብላቴናይቱም ሮጠች፥ ለእናትዋም ቤት ይህን ነገር ሁሉ ተናገረች።

28 And the damsel ran, and told them of her mother’s house these things.

29 ለርብቃም ላባ የተባለ ወንድም ነበራት ላባም ወደ ውጪ ወደ ውኃው ምንጭ ወደ ሰውዮው ሮጠ።

29 And Rebekah had a brother, and his name was Laban: and Laban ran out unto the man, unto the well.

30 ቀለበቱንና አምባሮቹን በእኅቱ እጅ ባየ ጊዜ፥ የእኅቱን የርብቃንም ነገር፦ ያ ሰው እንዲህ አለኝ ያለችውን በሰማ ጊዜ፥ እርሱ ወደዚያ ሰው መጣ እነሆም፥ በውኃው ምንጭ አጠገብ ከግመሎቹ ዘንድ ቆሞ ነበር።

30 And it came to pass, when he saw the earring and bracelets upon his sister’s hands, and when he heard the words of Rebekah his sister, saying, Thus spake the man unto me; that he came unto the man; and, behold, he stood by the camels at the well.

31 እርሱም አለው፦ አንተ የእግዚአብሔር ቡሩክ፥ ግባ ስለምን አንተ በውጪ ቆመሃል? እኔም ቤቱን ለግመሎችህም ስፍራ አዘጋጅቼአለሁ።

31 And he said, Come in, thou blessed of the Lord; wherefore standest thou without? for I have prepared the house, and room for the camels.

32 ሰውዮውም ወደ ቤት ገባ፥ ግመሎቹንም አራገፈ ገለባና ገፈራም ለግመሎቹ አቀረበ እግሩን ይታጠብ ዘንድ፥ ከእርሱም ጋር ላሉት ሰዎች እግር ውኃ አቀረበ።

32 And the man came into the house: and he ungirded his camels, and gave straw and provender for the camels, and water to wash his feet, and the men’s feet that were with him.

33 መብልንም በፊቱ አቀረበለት እርሱ ግን፦ ነገሬን እስክናገር ድረስ አልበላም አለ። እርሱም፦ ተናገር አለው።

33 And there was set meat before him to eat: but he said, I will not eat, until I have told mine errand. And he said, Speak on.

34 እርሱም አለ፦ እኔ የአብርሃም ሎሌ ነኝ።

34 And he said, I am Abraham’s servant.

35 እግዚአብሔርም ጌታዬን እጅግ ባረከው፥ አገነነውም በጎችንና ላሞችን፥ ብርንም፥ ወርቅንም፥ ወንዶች ባሪያዎችንና ሴቶች ባሪያዎችን፥ ግመሎችንም አህዮችንም ሰጠው።

35 And the Lord hath blessed my master greatly; and he is become great: and he hath given him flocks, and herds, and silver, and gold, and menservants, and maidservants, and camels, and asses.

36 ሣራም የጌታዬ ሚስት በእርጅናው ለጌታዬ ወንድ ልጅን ወለደች የነበረውንም ሁሉ ሰጠው።

36 And Sarah my master’s wife bare a son to my master when she was old: and unto him hath he given all that he hath.

37 ጌታዬም እንዲህ ሲል አማለኝ። እኔ ካለሁበት አገር ከከነዓናውያን ሴቶች ልጆች ለልጄ ሚስትን አትውሰድ

37 And my master made me swear, saying, Thou shalt not take a wife to my son of the daughters of the Canaanites, in whose land I dwell:

38 ነገር ግን ወደ አባቴ ቤት ወደ ወገኔም ሂድ፥ ለልጄም ሚስትን ውሰድለት።

38 But thou shalt go unto my father’s house, and to my kindred, and take a wife unto my son.

39 ጌታዬንም፦ ሴቲቱ ምናልባት ባትከተለኝሳ? አልሁት።

39 And I said unto my master, Peradventure the woman will not follow me.

40 እርሱም አለኝ፦ አካሄዴን በፊቱ ያደረግሁለት እግዚአብሔር መልአኩን ከአንተ ጋር ይልካል፥ መንገድህንም ያቀናል። ለልጄም ከወገኖቼ ከአባቴም ቤት ሚስትን ትወስዳለህ

40 And he said unto me, The Lord, before whom I walk, will send his angel with thee, and prosper thy way; and thou shalt take a wife for my son of my kindred, and of my father’s house:

41 የዚያን ጊዜ ከመሐላዬ ንጹሕ ነህ ወደ ዘመዶቼ ሄደህ እነርሱ ባይሰጡህ ካማልሁህ መሐላ ንጹሕ ትሆናለህ።

41 Then shalt thou be clear from this my oath, when thou comest to my kindred; and if they give not thee one, thou shalt be clear from my oath.

42 ዛሬም ወደ ውኃው ምንጭ መጣሁ፥ እንዲህም አልሁ። የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ዛሬ የምሄድበትን መንገዴን ብታቀናልኝ

42 And I came this day unto the well, and said, O Lord God of my master Abraham, if now thou do prosper my way which I go:

43 እነሆ፥ እኔ በውኃው ምንጭ ላይ ቆሜአለሁ ውኃ ልትቀዳ ለምትመጣውም ቆንጆ። ጥቂት ውኃ ከእንስራሽ አጠጪኝ ስላት፥

43 Behold, I stand by the well of water; and it shall come to pass, that when the virgin cometh forth to draw water, and I say to her, Give me, I pray thee, a little water of thy pitcher to drink;

44 እርስዋም፦ አንተ ጠጣ፥ ደግሞም ለግመሎችህ እቀዳለሁ የምትለኝ፥ እግዚአብሔር ለጌታዬ ልጅ ያዘጋጃት ሴት እርስዋ ትሁን።

44 And she say to me, Both drink thou, and I will also draw for thy camels: let the same be the woman whom the Lord hath appointed out for my master’s son.

45 እኔም የልቤን መናገር ገና ሳልፈጽም፥ እነሆ፥ ርብቃ እንስራዋን በትከሻዋ ተሸክማ ወጣች፥ ወደ ምንጭም ወርዳ ውኃ ቀዳች እኔም፦ እስኪ አጠጪኝ አልኋት።

45 And before I had done speaking in mine heart, behold, Rebekah came forth with her pitcher on her shoulder; and she went down unto the well, and drew water: and I said unto her, Let me drink, I pray thee.

46 ፈጥናም እንስራዋን ከጫንቃዋ አወረደችና፦ አንተ ጠጣ፥ ግመሎችህንም ደግሞ አጠጣለሁ አለች እኔም ጠጣሁ፥ ግመሎቼንም ደግሞ አጠጣች።

46 And she made haste, and let down her pitcher from her shoulder, and said, Drink, and I will give thy camels drink also: so I drank, and she made the camels drink also.

47 እኔም፦ አንቺ የማን ልጅ ነሽ? ብዬ ጠየቅኋት። እርስዋም፦ ሚልካ ለናኮር የወለደችለት የባቱኤል ልጅ ነኝ አለች ቀለበትም አደረግሁላት፥ ለእጆችዋም አምባሮች አደረግሁላት።

47 And I asked her, and said, Whose daughter art thou? And she said, The daughter of Bethuel, Nahor’s son, whom Milcah bare unto him: and I put the earring upon her face, and the bracelets upon her hands.

48 በግምባሬም አጎነበስሁ፥ ለእግዚአብሔርም ሰገድሁ የጌታዬን የወንድሙን ልጅ ለልጁ እወስድ ዘንድ በቀና መንገድ የመራኝን የጌታዬን የአብርሃምን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገንሁ።

48 And I bowed down my head, and worshipped the Lord, and blessed the Lord God of my master Abraham, which had led me in the right way to take my master’s brother’s daughter unto his son.

49 አሁንም ቸርነትና እውነት ለጌታዬ ትሠሩ እንደ ሆነ ንገሩኝ ይህም ባይሆን ንገሩኝ፥ ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ እል ዘንድ።

49 And now if ye will deal kindly and truly with my master, tell me: and if not, tell me; that I may turn to the right hand, or to the left.

50 ላባና ባቱኤልም መለሱ እንዲህም አሉ፦ ነገሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቶአል ክፉም በጎም ልንመልስልህ አንችልም።

50 Then Laban and Bethuel answered and said, The thing proceedeth from the Lord: we cannot speak unto thee bad or good.

51 ርብቃ እንኋት በፊትህ ናት ይዘሃት ሂድ፥ እግዚአብሔር እንደ ተናገረ ለጌታህም ልጅ ሚስት ትሁን።

51 Behold, Rebekah is before thee, take her, and go, and let her be thy master’s son’s wife, as the Lord hath spoken.

52 የአብርሃምም ሎሌ ነገራቸውን በሰማ ጊዜ ወደ ምድር ወድቆ ለእግዚአብሔር ሰገደ።

52 And it came to pass, that, when Abraham’s servant heard their words, he worshipped the Lord, bowing himself to the earth.

53 ሎሌውም የብርና የወርቅ ጌጥ ልብስም አወጣ፥ ለርብቃም ሰጣት የከበረ ስጦታንም ለወንድምዋና ለእናትዋ አቀረበ።

53 And the servant brought forth jewels of silver, and jewels of gold, and raiment, and gave them to Rebekah: he gave also to her brother and to her mother precious things.

54 እርሱም ከእርሱም ጋር ያሉት በሉ ጠጡም፥ ከዚያም አደሩ ማልደውም ተነሡና፦ ወደ ጌታዬ እሄድ ዘንድ አሰናብቱኝ አላቸው።

54 And they did eat and drink, he and the men that were with him, and tarried all night; and they rose up in the morning, and he said, Send me away unto my master.

55 ወንድምዋና እናትዋም፦ ብላቴናይቱ አንድ አሥር ቀን ያህል እንኳ ከእኛ ዘንድ ትቀመጥ ከዚያም በኋላ ትሄዳለች አሉ።

55 And her brother and her mother said, Let the damsel abide with us a few days, at the least ten; after that she shall go.

56 እርሱም፦ እግዚአብሔር መንገዴን አቅንቶልኛልና አታዘግዩኝ ወደ ጌታዬ እሄድ ዘንድ አሰናብቱኝ አላቸው።

56 And he said unto them, Hinder me not, seeing the Lord hath prospered my way; send me away that I may go to my master.

57 እነርሱም፦ ብላቴናይቱን እንጥራና ከአፍዋ እንጠይቅ አሉ።

57 And they said, We will call the damsel, and enquire at her mouth.

58 ርብቃንም ጠርተው፦ ከዚህ ሰው ጋር ትሄጃለሽን? አሉአት። እርስዋም፦ እሄዳለሁ አለች።

58 And they called Rebekah, and said unto her, Wilt thou go with this man? And she said, I will go.

59 እኅታቸውንም ርብቃን ሞግዚትዋንም የአብርሃምን ሎሌና ሰዎቹንም አሰናበቱአቸው።

59 And they sent away Rebekah their sister, and her nurse, and Abraham’s servant, and his men.

60 ርብቃንም መረቁአትና፦ አንቺ እኅታችን፥ እልፍ አእላፋት ሁኚ ዘርሽም የጠላቶችን ደጅ ይውረስ አሉአት።

60 And they blessed Rebekah, and said unto her, Thou art our sister, be thou the mother of thousands of millions, and let thy seed possess the gate of those which hate them.

61 ርብቃም ተነሣች ደንገጥሮችዋም፥ በግመሎችም ላይ ተቀምጠው ያንን ሰው ተከተሉት ሎሌውም ርብቃን ተቀብሎ ሄደ።

61 And Rebekah arose, and her damsels, and they rode upon the camels, and followed the man: and the servant took Rebekah, and went his way.

62 ይስሐቅም ብኤርለሃይሮኢ በሚሉአት ምንጭ መንገድ መጣ በአዜብ ምድር ተቀምጦ ነበርና።

62 And Isaac came from the way of the well Lahai–roi; for he dwelt in the south country.

63 ይስሐቅም በመሸ ጊዜ በልቡ እያሰላሰለ ወደ ሜዳ ወጥቶ ነበር ዓይኖቹንም አቀና፥ እነሆም ግመሎች ሲመጡ አየ።

63 And Isaac went out to meditate in the field at the eventide: and he lifted up his eyes, and saw, and, behold, the camels were coming.

64 ርብቃም ዓይኖችዋን አቀናች፥ ይስሐቅንም አየች፥ ከግመልም ወረደች።

64 And Rebekah lifted up her eyes, and when she saw Isaac, she lighted off the camel.

65 ሎሌውንም፦ ሊገናኘን በሜዳ የሚመጣ ይህ ሰው ማን ነው? አለችው። ሎሌውም፦ እርሱ ጌታዬ ነው አላት እርስዋም መሸፈኛ ወስዳ ተከናነበች።

65 For she had said unto the servant, What man is this that walketh in the field to meet us? And the servant had said, It is my master: therefore she took a vail, and covered herself.

66 ሎሌውም ያደረገውን ነገር ሁሉ ለይስሐቅ ነገረው።

66 And the servant told Isaac all things that he had done.

67 ይስሐቅም ወደ እናቱ ወደ ሣራ ድንኳን አገባት፥ ርብቃንም ወሰዳት፥ ሚስትም ሆነችው፥ ወደዳትም ይስሐቅም ከእናቱ ሞት ተጽናና።

67 And Isaac brought her into his mother Sarah’s tent, and took Rebekah, and she became his wife; and he loved her: and Isaac was comforted after his mother’s death.