መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon
| Mishlei Shlomo #17
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መጽሐፈ ምሳሌ 17

Proverbs 17

1 ጥል ባለበት ዘንድ እርድ ከሞላበት ቤት በጸጥታ ደረቅ ቍራሽ ይሻላል።

1 Better is a dry morsel, and quietness therewith, than an house full of sacrifices with strife.

2 አስተዋይ ባሪያ ነውረኛውን ልጅ ይገዛል፥ በወንድማማች መካከልም ርስትን ይካፈላል።

2 A wise servant shall have rule over a son that causeth shame, and shall have part of the inheritance among the brethren.

3 ማቅለጫ ለብር፥ ከውር ለወርቅ ነው እግዚአብሔር ግን ልብን ይፈትናል።

3 The fining pot is for silver, and the furnace for gold: but the Lord trieth the hearts.

4 ክፉ ሰው የበደለኛን ከንፈር ይሰማል ሐሰተኛም ወደ ተንኰለኛ ምላስ ያደምጣል።

4 A wicked doer giveth heed to false lips; and a liar giveth ear to a naughty tongue.

5 በድሀ የሚያላግጥ ፈጣሪውን ይሰድባል በጥፋትም ደስ የሚለው ሳይቀጣ አይቀርም።

5 Whoso mocketh the poor reproacheth his Maker: and he that is glad at calamities shall not be unpunished.

6 የሽማግሌዎች አክሊል የልጅ ልጆች ናቸው የልጆችም ክብር አባቶቻቸው ናቸው።

6 Children’s children are the crown of old men; and the glory of children are their fathers.

7 ለሰነፍ የኵራት አነጋገር አይገባውም ይልቁንም ሐሰተኛ ከንፈር ለመኰንን አይገባውም።

7 Excellent speech becometh not a fool: much less do lying lips a prince.

8 ገንዘብ ባደረገው ፊት መማለጃ እንደ ተዋበ ዕንቍ ነው፥ ወደ ዞረበትም ስፍራ ሁሉ ሥራውን ያቀናል።

8 A gift is as a precious stone in the eyes of him that hath it: whithersoever it turneth, it prospereth.

9 ኃጢአትን የሚከድን ሰው ፍቅርን ይሻል ነገርን የሚደጋግም ግን የተማመኑትን ወዳጆቹን ይለያያል።

9 He that covereth a transgression seeketh love; but he that repeateth a matter separateth very friends.

10 መቶ ግርፋት በሰነፍ ጠልቆ ከሚገባ ይልቅ ተግሣጽ በአስተዋይ ሰው ጠልቆ ወደ ልቡ ይገባል።

10 A reproof entereth more into a wise man than an hundred stripes into a fool.

11 ክፉ ሰው ዓመፃን ብቻ ይሻል ስለዚህ ጨካኝ መልአክ ይላክበታል።

11 An evil man seeketh only rebellion: therefore a cruel messenger shall be sent against him.

12 ሰነፍን በስንፍናው ከመገናኘት ልጆችዋ የተነጠቁባትን ድብ መገናኘት ይሻላል።

12 Let a bear robbed of her whelps meet a man, rather than a fool in his folly.

13 በመልካም ፋንታ ክፉን የሚመልስ፥ ክፉ ነገር ከቤቱ አትርቅም።

13 Whoso rewardeth evil for good, evil shall not depart from his house.

14 የጠብ መጀመሪያ እንደ ውኃ አፈሳሰስ ነው ስለዚህ ጠብ ሳይበረታ አንተ ክርክርን ተው።

14 The beginning of strife is as when one letteth out water: therefore leave off contention, before it be meddled with.

15 ኀጥኡን የሚያጸድቅና በጻድቁ ላይ የሚፈርድ፥ ሁለቱ በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊዎች ናቸው።

15 He that justifieth the wicked, and he that condemneth the just, even they both are abomination to the Lord.

16 በሰነፍ እጅ የጥበብ መግዣ ገንዘብ መኖሩ ስለ ምንድር ነው? ጥበብን ይገዛ ዘንድ አእምሮ የለውምና።

16 Wherefore is there a price in the hand of a fool to get wisdom, seeing he hath no heart to it?

17 ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳል ወንድምም ለመከራ ይወለዳል።

17 A friend loveth at all times, and a brother is born for adversity.

18 አእምሮ የጐደለው ሰው አጋና ይመታል፥ በባልንጀራውም ፊት ይዋሳል።

18 A man void of understanding striketh hands, and becometh surety in the presence of his friend.

19 ዓመፃን የሚወድድ ክርክርን ይወድዳል ደጁንም ዘለግ የሚያደርግ ውድቀትን ይሻል።

19 He loveth transgression that loveth strife: and he that exalteth his gate seeketh destruction.

20 ጠማማ ልብ ያለው መልካምን አያገኝም፥ ምላሱንም የሚገለብጥ በክፉ ላይ ይወድቃል።

20 He that hath a froward heart findeth no good: and he that hath a perverse tongue falleth into mischief.

21 ሰነፍን የሚወልድ ኀዘን ይሆንበታል፥ የደንቆሮ ልጅም አባት ደስ አይለውም።

21 He that begetteth a fool doeth it to his sorrow: and the father of a fool hath no joy.

22 ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች።

22 A merry heart doeth good like a medicine: but a broken spirit drieth the bones.

23 ኀጥእ የፍርድን መንገድ ለማጥመም ከብብት መማለጃን ይወስዳል።

23 A wicked man taketh a gift out of the bosom to pervert the ways of judgment.

24 በአስተዋይ ፊት ጥበብ ትኖራለች የሰነፍ ዓይን ግን በምድር ዳርቻ ነው።

24 Wisdom is before him that hath understanding; but the eyes of a fool are in the ends of the earth.

25 ሰነፍ ልጅ ለአባቱ ፀፀት ነው፥ ለወለደችውም ምሬት ነው።

25 A foolish son is a grief to his father, and bitterness to her that bare him.

26 ጻድቅን መቅጣት፥ ጨዋ ሰውንም በጻድቅነቱ መምታት መልካም አይደለም።

26 Also to punish the just is not good, nor to strike princes for equity.

27 ጥቂት ቃልን የሚናገር አዋቂ ነው፥ መንፈሱም ቀዝቃዛ የሆነ አስተዋይ ነው።

27 He that hath knowledge spareth his words: and a man of understanding is of an excellent spirit.

28 ሰነፍ ዝም ቢል ጠቢብ ሆኖ ይቈጠራል፥ ከንፈሩንም የሚቈልፍ። ባለ አእምሮ ነው ይባላል።

28 Even a fool, when he holdeth his peace, is counted wise: and he that shutteth his lips is esteemed a man of understanding.