መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon
| Mishlei Shlomo #18
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መጽሐፈ ምሳሌ 18

Proverbs 18

1 መለየት የሚወድድ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል።

1 Through desire a man, having separated himself, seeketh and intermeddleth with all wisdom.

2 ሰነፍ የጥበብን ነገር አይወድድም በልቡ ያለውን ሁሉ መግለጥ ብቻ ይወድዳል እንጂ።

2 A fool hath no delight in understanding, but that his heart may discover itself.

3 ኀጥእ በመጣ ጊዜ ንቀት ደግሞ ይመጣል፥ ነውርም ከስድብ ጋር።

3 When the wicked cometh, then cometh also contempt, and with ignominy reproach.

4 የሰው አፍ ቃል የጠለቀ ውኃ ነው፥ የጥበብም ምንጭ ፈሳሽ ወንዝ ነው።

4 The words of a man’s mouth are as deep waters, and the wellspring of wisdom as a flowing brook.

5 የጻድቅ ፍርድ ይጠምም ዘንድ፥ ለኀጥእም ማድላት መልካም አይደለም።

5 It is not good to accept the person of the wicked, to overthrow the righteous in judgment.

6 የሰነፍ ከንፈር በጥል ውስጥ ትገባለች፥ አፉም በትርን ትጠራለች።

6 A fool’s lips enter into contention, and his mouth calleth for strokes.

7 የሰነፍ አፍ ለራሱ ጥፋት ነው፥ ከንፈሩም ለነፍሱ ወጥመድ ነው።

7 A fool’s mouth is his destruction, and his lips are the snare of his soul.

8 የጆሮ ጠቢ ቃል እንደ ጣፋጭ መብል ነው፥ እርሱም እስከ ሆድ ጕርጆች ድረስ ይወርዳል።

8 The words of a talebearer are as wounds, and they go down into the innermost parts of the belly.

9 በሥራው ታካች የሚሆን የሀብት አጥፊ ወንድም ነው።

9 He also that is slothful in his work is brother to him that is a great waster.

10 የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው ጻድቅ ወደ እርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።

10 The name of the Lord is a strong tower: the righteous runneth into it, and is safe.

11 ለባለጠጋ ሰው ሀብቱ እንደ ጸናች ከተማ ናት፥ በአሳቡም እንደ ረጅም ቅጥር።

11 The rich man’s wealth is his strong city, and as an high wall in his own conceit.

12 ሰው ሳይወድቅ በፊት ልቡ ከፍ ከፍ ይላል፥ ትሕትናም ክብረትን ትቀድማለች።

12 Before destruction the heart of man is haughty, and before honour is humility.

13 ሳይሰማ ነገርን በሚመልስ ስንፍናና እፍረት ይሆንበታል።

13 He that answereth a matter before he heareth it, it is folly and shame unto him.

14 የሰው ነፍስ ሕመሙን ይታገሣል የተቀጠቀጠን መንፈስ ግን ማን ያጠንክረዋል?

14 The spirit of a man will sustain his infirmity; but a wounded spirit who can bear?

15 የአስተዋይ ልብ እውቀትን ያገኛል፥ የጠቢባንም ጆሮ እውቀትን ትፈልጋለች።

15 The heart of the prudent getteth knowledge; and the ear of the wise seeketh knowledge.

16 የሰው ስጦታ መንገዱን ታሰፋለታለች፥ በታላላቆችም ፊት ታገባዋለች።

16 A man’s gift maketh room for him, and bringeth him before great men.

17 ወደ ፍርድ አስቀድሞ የገባ ጻድቅ ይመስላል ባልንጀራው ግን መጥቶ ይመረምረዋል።

17 He that is first in his own cause seemeth just; but his neighbour cometh and searcheth him.

18 ዕጣ ክርክርን ትከለክላለች፥ በኃያላንም መካከል ትበይናለች።

18 The lot causeth contentions to cease, and parteth between the mighty.

19 የተበደለ ወንድም እንደ ጸናች ከተማ ጽኑ ነው ክርክራቸውም እንደ ግንብ ብረት ነው።

19 A brother offended is harder to be won than a strong city: and their contentions are like the bars of a castle.

20 የሰው ሆድ ከአፉ ፍሬ ይሞላል ከንፈሩም ከሚያፈራው ይጠግባል።

20 A man’s belly shall be satisfied with the fruit of his mouth; and with the increase of his lips shall he be filled.

21 ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ።

21 Death and life are in the power of the tongue: and they that love it shall eat the fruit thereof.

22 ሚስት ያገኘ በረከትን አገኘ፥ ከእግዚአብሔርም ሞገስን ይቀበላል።

22 Whoso findeth a wife findeth a good thing, and obtaineth favour of the Lord.

23 ድሀ በትሕትና እየለመነ ይናገራል ባለጠጋ ግን በድፍረት ይመልሳል።

23 The poor useth intreaties; but the rich answereth roughly.

24 ብዙ ወዳጆች ያሉት ሰው ይጠፋል ነገር ግን ከወንድም አብልጦ የሚጠጋጋ ወዳጅ አለ።

24 A man that hath friends must shew himself friendly: and there is a friend that sticketh closer than a brother.