መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon | Mishlei Shlomo #13
In Amharic and English
መጽሐፈ ምሳሌ 13 |
Proverbs 13 |
1 ባለ አእምሮ ልጅ የአባቱን ተግሣጽ ይሰማል። ፌዘኛ ግን ተግሣጽን አይሰማም። |
1 A wise son heareth his father’s instruction: but a scorner heareth not rebuke. |
2 ሰው ከአፉ ፍሬ መልካምን ይበላል የዓመፀኞች ነፍስ ግን ግፍን ትሻለች። |
2 A man shall eat good by the fruit of his mouth: but the soul of the transgressors shall eat violence. |
3 አፉን የሚጠብቅ ነፍሱን ይጠብቃል ከንፈሩን የሚያሞጠሙጥ ግን ጥፋትን ያገኘዋል። |
3 He that keepeth his mouth keepeth his life: but he that openeth wide his lips shall have destruction. |
4 የታካች ሰው ነፍስ ትመኛለች አንዳችም አታገኝም የትጉ ነፍስ ግን ትጠግባለች። |
4 The soul of the sluggard desireth, and hath nothing: but the soul of the diligent shall be made fat. |
5 ጻድቅ ሐሰትን ይጠላል ኀጥእ ግን ያሳፍራል ያስነውራልም። |
5 A righteous man hateth lying: but a wicked man is loathsome, and cometh to shame. |
6 በመንገዱ ያለ ነውር የሚሄደውን ጽድቅ ይጠብቀዋል ኃጢአት ግን ኃጢአተኛውን ይጥለዋል። |
6 Righteousness keepeth him that is upright in the way: but wickedness overthroweth the sinner. |
7 ራሱን ባለጠጋ የሚያስመስል ሰው አለ፥ ነገር ግን አንዳች የለውም ራሱን ድሀ የሚያስመስል አለ፥ ነገር ግን እጅግ ባለጠግነት አለው። |
7 There is that maketh himself rich, yet hath nothing: there is that maketh himself poor, yet hath great riches. |
8 ለሰው ነፍስ ቤዛው ሀብቱ ነው ድሀ ግን ተግሣጽን አይሰማም። |
8 The ransom of a man’s life are his riches: but the poor heareth not rebuke. |
9 ሁልጊዜ ለጻድቃን ብርሃን ነው የኀጥኣን መብራት ግን ይጠፋል። |
9 The light of the righteous rejoiceth: but the lamp of the wicked shall be put out. |
10 በትዕቢት ጠብ ብቻ ይሆናል ጥበብ ግን ምክርን በሚቀበሉ ዘንድ ናት። |
10 Only by pride cometh contention: but with the well advised is wisdom. |
11 በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። |
11 Wealth gotten by vanity shall be diminished: but he that gathereth by labour shall increase. |
12 የምትዘገይ ተስፋ ልብን ታሳዝናለች የተገኘች ፈቃድ ግን የሕይወት ዛፍ ናት። |
12 Hope deferred maketh the heart sick: but when the desire cometh, it is a tree of life. |
13 ትእዛዝን የሚያቃልል በትእዛዝ ተይዞ ይጠፋል ትእዛዝን የሚፈራ ግን በደኅንነት ይኖራል። |
13 Whoso despiseth the word shall be destroyed: but he that feareth the commandment shall be rewarded. |
14 ሰው ከሞት ወጥመድ ያመልጥ ዘንድ የጠቢብ ሰው ትምህርት የሕይወት ምንጭ ነው። |
14 The law of the wise is a fountain of life, to depart from the snares of death. |
15 መልካም እውቀት ሞገስን ይሰጣል የወስላቶች መንገድ ግን ሸካራ ናት። |
15 Good understanding giveth favour: but the way of transgressors is hard. |
16 ብልህ ሁሉ በእውቀት ይሠራል ሰነፍ ግን ስንፍናውን ይገልጣል። |
16 Every prudent man dealeth with knowledge: but a fool layeth open his folly. |
17 መጥፎ መልእክተኛ በክፉ ላይ ይወድቃል የታመነ መልእክተኛ ግን ፈውስ ነው። |
17 A wicked messenger falleth into mischief: but a faithful ambassador is health. |
18 ድህነትና ነውር ተግሣጽን ቸል ለሚሉ ነው ዘለፋን የሚሰማ ግን ይከብራል። |
18 Poverty and shame shall be to him that refuseth instruction: but he that regardeth reproof shall be honoured. |
19 የተፈጸመች ፈቃድ ሰውነትን ደስ ታሰኛለች ሰነፎች ግን ከክፉ መራቅን ይጸየፋሉ። |
19 The desire accomplished is sweet to the soul: but it is abomination to fools to depart from evil. |
20 ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል የሰነፎች ባልንጀራ ግን ክፉ መከራን ይቀበላል። |
20 He that walketh with wise men shall be wise: but a companion of fools shall be destroyed. |
21 ክፉ ነገር ኃጢአተኞችን ያሳድዳቸዋል ጻድቃን ግን መልካሙን ዋጋ ይቀበላሉ። |
21 Evil pursueth sinners: but to the righteous good shall be repayed. |
22 ጻድቅ ሰው ለልጅ ልጆቹ ያወርሳል የኃጢአተኛ ብልጥግና ግን ለጻድቅ ትጠበቃለች። |
22 A good man leaveth an inheritance to his children’s children: and the wealth of the sinner is laid up for the just. |
23 በድሆች እርሻ ላይ ብዙ ሲሳይ አለ ከፍርድ መጕደል የተነሣ ግን ይጠፋል። |
23 Much food is in the tillage of the poor: but there is that is destroyed for want of judgment. |
24 በበትር ከመምታት የሚራራ ሰው ልጁን ይጠላል ልጁን የሚወድድ ግን ተግቶ ይገሥጻዋል። |
24 He that spareth his rod hateth his son: but he that loveth him chasteneth him betimes. |
25 ጻድቅ ሰውነቱ እስክትጠግብ ድረስ ይበላል የኀጥኣን ሆድ ግን ይራባል። |
25 The righteous eateth to the satisfying of his soul: but the belly of the wicked shall want. |