መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #121
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 121

Psalm 121

1 ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ?

1 I will lift up mine eyes unto the hills, from whence cometh my help.

2 ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

2 My help cometh from the Lord, which made heaven and earth.

3 እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም የሚጠብቅህም አይተኛም።

3 He will not suffer thy foot to be moved: he that keepeth thee will not slumber.

4 እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።

4 Behold, he that keepeth Israel shall neither slumber nor sleep.

5 እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል።

5 The Lord is thy keeper: the Lord is thy shade upon thy right hand.

6 ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት።

6 The sun shall not smite thee by day, nor the moon by night.

7 እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስህንም ይጠብቃታል።

7 The Lord shall preserve thee from all evil: he shall preserve thy soul.

8 ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል።

8 The Lord shall preserve thy going out and thy coming in from this time forth, and even for evermore.