መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #122
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 122

Psalm 122

1 ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።

1 I was glad when they said unto me, Let us go into the house of the Lord.

2 ኢየሩሳሌም ሆይ፥ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ።

2 Our feet shall stand within thy gates, O Jerusalem.

3 ኢየሩሳሌምስ እርስ በርስዋ እንደ ተገጠገጠች ከተማ ተሠርታለች።

3 Jerusalem is builded as a city that is compact together:

4 የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑ ዘንድ፥ ለእስራኤል ምስክር ሊሆኑ የእግዚአብሔር ነገዶች ወደዚያ ይወጣሉ።

4 Whither the tribes go up, the tribes of the Lord, unto the testimony of Israel, to give thanks unto the name of the Lord.

5 ዙፋኖች በዚያ ለፍርድ ተቀምጠዋልና፥ የዳዊት ቤት ዙፋኖች።

5 For there are set thrones of judgment, the thrones of the house of David.

6 ለኢየሩሳሌም ሰላምን ለምኑ አንተንም ለሚወድዱ ልማት ይሁን።

6 Pray for the peace of Jerusalem: they shall prosper that love thee.

7 በኃይልህ ሰላም፥ በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን።

7 Peace be within thy walls, and prosperity within thy palaces.

8 ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም፥ በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ።

8 For my brethren and companions’ sakes, I will now say, Peace be within thee.

9 ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ።

9 Because of the house of the Lord our God I will seek thy good.