መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #148
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 148

Psalm 148

1 ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት በአርያም አመስግኑት።

1 Praise ye the Lord. Praise ye the Lord from the heavens: praise him in the heights.

2 መላእክቱ ሁሉ፥ አመስግኑት ሠራዊቱ ሁሉ፥ አመስግኑት።

2 Praise ye him, all his angels: praise ye him, all his hosts.

3 ፀሐይና ጨረቃ፥ አመስግኑት ከዋክብትና ብርሃን ሁሉ፥ አመስግኑት።

3 Praise ye him, sun and moon: praise him, all ye stars of light.

4 ሰማየ ሰማያት፥ አመስግኑት የሰማያት በላይም ውኃ።

4 Praise him, ye heavens of heavens, and ye waters that be above the heavens.

5 እርሱ ብሎአልና፥ ሆኑም እርሱም አዝዞአልና፥ ተፈጠሩም የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑት።

5 Let them praise the name of the Lord: for he commanded, and they were created.

6 ለዘላለም ዓለም አቆማቸው ትእዛዝን ሰጠ፥ አያልፉምም።

6 He hath also stablished them for ever and ever: he hath made a decree which shall not pass.

7 እባቦች ጥልቆችም ሁሉ፥ እግዚአብሔርን ከምድር አመስግኑት

7 Praise the Lord from the earth, ye dragons, and all deeps:

8 እሳትና በረዶ አመዳይና ውርጭ፥ ቃሉን የሚያደርግ ዐውሎ ነፋስም

8 Fire, and hail; snow, and vapour; stormy wind fulfilling his word:

9 ተራሮች ኰረብቶችም ሁሉ፥ የሚያፈራም ዛፍ ዝግባም ሁሉ

9 Mountains, and all hills; fruitful trees, and all cedars:

10 አራዊትም እንስሳትም ሁሉ፥ ተንቀሳቃሾችም የሚበርሩ ወፎችም

10 Beasts, and all cattle; creeping things, and flying fowl:

11 የምድር ነገሥታት አሕዛብም ሁሉ፥ አለቆች የምድርም ፈራጆች ሁሉ፥

11 Kings of the earth, and all people; princes, and all judges of the earth:

12 ጕልማሶችና ቈነጃጅቶች፥ ሽማግሌዎችና ልጆች

12 Both young men, and maidens; old men, and children:

13 የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑ ስሙ ብቻውን ከፍ ከፍ ብሎአልና፥ ምስጋናውም በሰማይና በምድር ላይ ነው።

13 Let them praise the name of the Lord: for his name alone is excellent; his glory is above the earth and heaven.

14 የሕዝቡንም ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል የቅዱሳኑንም ሁሉ ምስጋና ወደ እርሱ ለቀረበ ለእስራኤል ልጆች ሕዝብ ከፍ ከፍ ያደርጋል። ሃሌ ሉያ።

14 He also exalteth the horn of his people, the praise of all his saints; even of the children of Israel, a people near unto him. Praise ye the Lord.