መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #49
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 49

Psalm 49

1 አሕዛብ ሁላችሁ፥ ይህን ስሙ በዓለም የምትኖሩትም ሁላችሁ፥ አድምጡ

1 Hear this, all ye people; give ear, all ye inhabitants of the world:

2 ዝቅተኞችና ከፍተኞች፥ ባለጠጎችና ድሆች በአንድነት።

2 Both low and high, rich and poor, together.

3 አፌ ጥበብን ይናገራል፥ የልቤም አሳብ ማስተዋልን።

3 My mouth shall speak of wisdom; and the meditation of my heart shall be of understanding.

4 ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ፥ በበገናም ምሥጢሬን እገልጣለሁ።

4 I will incline mine ear to a parable: I will open my dark saying upon the harp.

5 ኃጢአት ተረከዜን በከበበኝ ጊዜ በክፉ ቀን ለምን እፈራለሁ?

5 Wherefore should I fear in the days of evil, when the iniquity of my heels shall compass me about?

6 በኃይላቸው የሚታመኑ፥ በባለጠግነታቸውም ብዛት የሚመኩ

6 They that trust in their wealth, and boast themselves in the multitude of their riches;

7 ወንድም ወንድሙን አያድንም፥ ሰውም አያድንም ቤዛውን ለእግዚአብሔር አይሰጥም፥

7 None of them can by any means redeem his brother, nor give to God a ransom for him:

8-9 ለዘላለም እንዲኖር፥ ጥፋትንም እንዳያይ የነፍሳቸው ለውጥ ከብሮአልና፥ ለዘላለምም ቀርቶአልና።

8 (For the redemption of their soul is precious, and it ceaseth for ever:)
9 That he should still live for ever, and not see corruption.

10 ብልሃተኞች እንዲሞቱ፥ ሰነፎችችና ደንቆሮች በአንድነት እንዲጠፉ፥ ገንዘባቸውንም ለሌሎች እንዲተዉ አይቶአል።

10 For he seeth that wise men die, likewise the fool and the brutish person perish, and leave their wealth to others.

11 በልባቸውም ቤታቸው ለዘላለም የሚኖር፥ ማደሪያቸውም ለልጆች ልጅ የሚሆን ይመስላቸዋል በየአገራቸውም ስማቸው ይጠራል።

11 Their inward thought is, that their houses shall continue for ever, and their dwelling places to all generations; they call their lands after their own names.

12 ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ።

12 Nevertheless man being in honour abideth not: he is like the beasts that perish.

13 ይህች መንገዳቸው መሰናክላቸው ናት፥ ከእነርሱም በኋላ የሚመጡ በአፋቸው እሺ ይላሉ።

13 This their way is their folly: yet their posterity approve their sayings. Selah.

14 እንደ በጎች ወደ ሲኦል የሚሄዱ ናቸው፥ እረኛቸውም ሞት ነው ቅኖችንም በማለዳ ይገዙአቸዋል፥ ውበታቸውም ከመኖሪያቸው ተለይታ በሲኦል ታረጃለች።

14 Like sheep they are laid in the grave; death shall feed on them; and the upright shall have dominion over them in the morning; and their beauty shall consume in the grave from their dwelling.

15 ነገር ግን እግዚአብሔር ይቀበለኛልና ነፍሴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል።

15 But God will redeem my soul from the power of the grave: for he shall receive me. Selah.

16 የሰው ባለጠግነት የቤቱም ክብር በበዛ ጊዜ አትፍራ፥

16 Be not thou afraid when one is made rich, when the glory of his house is increased;

17 በሞተ ጊዜ ከእርሱ ጋር ምንም አይወስድምና፥ ክብሩም ከእርሱ በኋላ አይወርድምና።

17 For when he dieth he shall carry nothing away: his glory shall not descend after him.

18 በሕይወቱ ሳለ ነፍሱን ባርኮአልና ለሰውነቱ መልካም ብታደርግለት ያመሰግንሃል።

18 Though while he lived he blessed his soul: and men will praise thee, when thou doest well to thyself.

19 ሆኖም ወደ አባቶቹ ትውልድ ይወርዳል ለዘላለም ብርሃንን አያይም።

19 He shall go to the generation of his fathers; they shall never see light.

20 አእምሮ የሌለው ክቡር ሰው እንደሚጠፋ እንስሶች መሰለ።

20 Man that is in honour, and understandeth not, is like the beasts that perish.