መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #50
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 50 |
Psalm 50 |
1 የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ተናገረ፥ ከፀሓይም መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ምድርን ጠራት። |
1 The mighty God, even the Lord, hath spoken, and called the earth from the rising of the sun unto the going down thereof. |
2 ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። |
2 Out of Zion, the perfection of beauty, God hath shined. |
3 አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ። |
3 Our God shall come, and shall not keep silence: a fire shall devour before him, and it shall be very tempestuous round about him. |
4 በላይ ያለውን ሰማይን ምድርንም በሕዝቡ ለመፍረድ ይጠራል |
4 He shall call to the heavens from above, and to the earth, that he may judge his people. |
5 ከእርሱ ጋር ለመሥዋዕት ኪዳን የቆሙትን ቅዱሳኑን ሰብስቡለት። |
5 Gather my saints together unto me; those that have made a covenant with me by sacrifice. |
6 ሰማያት ጽድቁን ይናገራሉ፥ እግዚአብሔር ፈራጅ ነውና። |
6 And the heavens shall declare his righteousness: for God is judge himself. Selah. |
7 ሕዝቤ፥ ስማኝ፥ ልንገርህ እስራኤልም፥ ስማኝ፥ ልመስክርብህ አምላክስ እኔ አምላክህ ነኝ። |
7 Hear, O my people, and I will speak; O Israel, and I will testify against thee: I am God, even thy God. |
8 ስለ ቍርባንህ የምዘልፍህ አይደለሁም የሚቃጠል መሥዋዕትህ ሁልጊዜ በፊቴ ነው። |
8 I will not reprove thee for thy sacrifices or thy burnt offerings, to have been continually before me. |
9 ከቤትህ ፍሪዳን ከመንጋህም አውራ ፍየልን አልወስድም |
9 I will take no bullock out of thy house, nor he goats out of thy folds. |
10 የምድረ በዳ አራዊት ሁሉ በሺህ ተራራዎች ያሉ እንስሶችም የእኔ ናቸውና። |
10 For every beast of the forest is mine, and the cattle upon a thousand hills. |
11 የሰማይን አዕዋፍ ሁሉ አውቃለሁ፥ የምድረ በዳ አራዊትም በእኔ ዘንድ ናቸው። |
11 I know all the fowls of the mountains: and the wild beasts of the field are mine. |
12 ብራብም ለአንተ አልነግርህም፥ ዓለምና ሞላው የእኔ ነውና። |
12 If I were hungry, I would not tell thee: for the world is mine, and the fulness thereof. |
13 የፍሪዳውን ሥጋ እበላለሁን? የፍየሉንስ ደም እጠጣለሁን? |
13 Will I eat the flesh of bulls, or drink the blood of goats? |
14 ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ሠዋ፥ ለልዑልም ስእለትህን ስጥ |
14 Offer unto God thanksgiving; and pay thy vows unto the most High: |
15 በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ። |
15 And call upon me in the day of trouble: I will deliver thee, and thou shalt glorify me. |
16 ኃጢአተኛውን ግን እግዚአብሔር አለው። ለምን አንተ ሕጌን ትናገራለህ? ኪዳኔንም በአፍህ ለምን ትወስዳለህ? |
16 But unto the wicked God saith, What hast thou to do to declare my statutes, or that thou shouldest take my covenant in thy mouth? |
17 አንተስ ተግሣጼን ጠላህ፥ ቃሎቼንም ወደ ኋላህ ጣልህ። |
17 Seeing thou hatest instruction, and castest my words behind thee. |
18 ሌባውን ባየህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ትሮጥ ነበር እድል ፈንታህንም ከአመንዝሮች ጋር አደረግህ። |
18 When thou sawest a thief, then thou consentedst with him, and hast been partaker with adulterers. |
19 አፍህ ክፋትን አበዛ፥ አንደበትህም ሽንገላን ተበተበ። |
19 Thou givest thy mouth to evil, and thy tongue frameth deceit. |
20 ተቀምጠህ ወንድምህን አማኸው፥ ለእናትህም ልጅ ዕንቅፋት አኖርህ። |
20 Thou sittest and speakest against thy brother; thou slanderest thine own mother’s son. |
21 ይህን አድርገህ ዝም አልሁህ እኔ እንደ አንተ እሆን ዘንድ ጠረጠርህ እዘልፍሃለሁ በፊትህም እቆማለሁ። |
21 These things hast thou done, and I kept silence; thou thoughtest that I was altogether such an one as thyself: but I will reprove thee, and set them in order before thine eyes. |
22 እግዚአብሔርን የምትረሱ እናንተ፥ ይህን አስተውሉ አለዚያ ግን ይነጥቃል የሚያድንም የለም። |
22 Now consider this, ye that forget God, lest I tear you in pieces, and there be none to deliver. |
23 ምስጋና የሚሠዋ ያከብረኛል የእግዚአብሔርን ማዳን ለእርሱ የማሳይበት መንገድ ከዚያ አለ። |
23 Whoso offereth praise glorifieth me: and to him that ordereth his conversation aright will I shew the salvation of God. |