መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon | Mishlei Shlomo #28
In Amharic and English
መጽሐፈ ምሳሌ 28 |
Proverbs 28 |
1 ኀጥእ ማንም ሳያሳድደው ይሸሻል ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ያለ ፍርሃት ይኖራል። |
1 The wicked flee when no man pursueth: but the righteous are bold as a lion. |
2 ስለ አገሪቱ ዓመፀኝነት አለቆችዋ ብዙ ሆኑ በአስተዋይና በአዋቂ ሰው ግን ዘመንዋ ይረዝማል። |
2 For the transgression of a land many are the princes thereof: but by a man of understanding and knowledge the state thereof shall be prolonged. |
3 ድሆችን የሚያስጨንቅ ምስኪን ሰው እህልን እንደሚያጠፋ እንደ ዶፍ ዝናብ ነው። |
3 A poor man that oppresseth the poor is like a sweeping rain which leaveth no food. |
4 ሕግን የሚተዉ ሰዎች ኀጥኣንን ያመሰግናሉ ሕግ ጠባቂዎች ግን ይጠሉአቸዋል። |
4 They that forsake the law praise the wicked: but such as keep the law contend with them. |
5 ክፉዎች ሰዎች ፍርድን አያስተውሉም እግዚአብሔርን የሚሹ ግን ሁሉን ያስተውላሉ። |
5 Evil men understand not judgment: but they that seek the Lord understand all things. |
6 በጠማማ መንገድ ከሚሄድ ባለጠጋ ያለ ነውር የሚሄድ ድሀ ይሻላል። |
6 Better is the poor that walketh in his uprightness, than he that is perverse in his ways, though he be rich. |
7 ሕግን የሚጠብቅ አስተዋይ ልጅ ነው ምናምንቴዎችን የሚከተል ግን አባቱን ያሳፍራል። |
7 Whoso keepeth the law is a wise son: but he that is a companion of riotous men shameth his father. |
8 በአራጣ ብዛትና በቅሚያ ሀብቱን የሚያበዛ ለድሀ ለሚራራ ያከማችለታል። |
8 He that by usury and unjust gain increaseth his substance, he shall gather it for him that will pity the poor. |
9 ሕግን ከመስማት ጆሮውን የሚመልስ ጸሎቱ አስጸያፊ ናት። |
9 He that turneth away his ear from hearing the law, even his prayer shall be abomination. |
10 ቅኖችን በክፉ መንገድ የሚያስት፥ እርሱ ወደ ጕድጓዱ ይወድቃል ፍጹማን ግን መልካም ነገርን ይወርሳሉ። |
10 Whoso causeth the righteous to go astray in an evil way, he shall fall himself into his own pit: but the upright shall have good things in possession. |
11 ባለጠጋ ሰው ለራሱ ጠቢብ የሆነ ይመስለዋል አስተዋይ ድሀ ግን ይመረምረዋል። |
11 The rich man is wise in his own conceit; but the poor that hath understanding searcheth him out. |
12 ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ ኀጥኣን ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ ግን ሰው ይሸሸጋል። |
12 When righteous men do rejoice, there is great glory: but when the wicked rise, a man is hidden. |
13 ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል። |
13 He that covereth his sins shall not prosper: but whoso confesseth and forsaketh them shall have mercy. |
14 ሁልጊዜ የሚፈራ ሰው ምስጉን ነው ልቡን የሚያጸና ግን በክፉ ላይ ይወድቃል። |
14 Happy is the man that feareth alway: but he that hardeneth his heart shall fall into mischief. |
15 በድሀ ሕዝብ ላይ የሚገዛ ክፉ መኰንን እንደሚያገሣ አንበሳን እንደ ተራበ ድብ ነው። |
15 As a roaring lion, and a ranging bear; so is a wicked ruler over the poor people. |
16 አእምሮ የጐደለው መኰንን ትልቅ ግፈኛ ነው ግፍን የሚጠላ ግን ብዙ ዘመን ይኖራል። |
16 The prince that wanteth understanding is also a great oppressor: but he that hateth covetousness shall prolong his days. |
17 የሰው ደም ያለበት ሰው እንደ ጕድጓድ ይሸሻል፥ ማንም አያስጠጋውም። |
17 A man that doeth violence to the blood of any person shall flee to the pit; let no man stay him. |
18 በቅንነት የሚሄድ ይድናል በጠማምነት የሚሄድ ግን ወዲያው ይወድቃል። |
18 Whoso walketh uprightly shall be saved: but he that is perverse in his ways shall fall at once. |
19 ምድሩን የሚያርስ እንጀራ ይጠግባል ምናምንቴዎችን የሚከተል ግን ድህነት ይሞላበታል። |
19 He that tilleth his land shall have plenty of bread: but he that followeth after vain persons shall have poverty enough. |
20 የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። |
20 A faithful man shall abound with blessings: but he that maketh haste to be rich shall not be innocent. |
21 ማድላት፥ በቍራሽ እንጀራም መበደል መልካም አይደለም። |
21 To have respect of persons is not good: for for a piece of bread that man will transgress. |
22 ምቀኛ ሰው ባለጠጋ ለመሆን ይቸኵላል ችጋርም እንደሚመጣበት አያውቅም። |
22 He that hasteth to be rich hath an evil eye, and considereth not that poverty shall come upon him. |
23 ምላሱን ከሚያጣፍጥ ይልቅ ሰውን የሚገሥጽ በኋላ ሞገስ ያገኛል። |
23 He that rebuketh a man afterwards shall find more favour than he that flattereth with the tongue. |
24 ከአባቱና ከእናቱ የሚሰርቅ። ኃጢአትን አልሠራሁም የሚልም የአጥፊ ባልንጀራ ነው። |
24 Whoso robbeth his father or his mother, and saith, It is no transgression; the same is the companion of a destroyer. |
25 የሚጐመጅ ሰው ክርክርን ያነሣሣል በእግዚአብሔር የሚታመን ግን ይጠግባል። |
25 He that is of a proud heart stirreth up strife: but he that putteth his trust in the Lord shall be made fat. |
26 በገዛ ልቡ የሚታመን ሰው ሰነፍ ነው በጥበብ የሚሄድ ግን ይድናል። |
26 He that trusteth in his own heart is a fool: but whoso walketh wisely, he shall be delivered. |
27 ለድሀ የሚሰጥ አያጣም ዓይኖቹን የሚጨፍን ግን እጅግ ይረገማል። |
27 He that giveth unto the poor shall not lack: but he that hideth his eyes shall have many a curse. |
28 ኀጥአን በተነሡ ጊዜ ሰዎች ይሸሸጋሉ እነርሱ በጠፉ ጊዜ ግን ጻድቃን ይበዛሉ። |
28 When the wicked rise, men hide themselves: but when they perish, the righteous increase. |