መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon | Mishlei Shlomo #8
In Amharic and English
መጽሐፈ ምሳሌ 8 |
Proverbs 8 |
1 በውኑ ጥበብ አትጮኽምን? ማስተዋልስ ድምፅዋን አትሰጥምን? |
1 Doth not wisdom cry? and understanding put forth her voice? |
2 በኮረብታ ላይ በመንገድ አጠገብ በጎዳና መካከል ትቆማለች። |
2 She standeth in the top of high places, by the way in the places of the paths. |
3 በበሩ አጠገብ በከተማይቱም መግቢያ፥ በደጁ መግቢያ ትጮኻለች። |
3 She crieth at the gates, at the entry of the city, at the coming in at the doors. |
4 እናንተ ሰዎች፥ እናንተን እጠራለሁ፥ ድምፄም ወደ ሰዎች ልጆች ነው። |
4 Unto you, O men, I call; and my voice is to the sons of man. |
5 እናንተ አላዋቂዎች፥ ብልሃትን አስተውሉ እናንተም ሰነፎች ጥበብን በልባችሁ ያዙ። |
5 O ye simple, understand wisdom: and, ye fools, be ye of an understanding heart. |
6 የከበረች ነገርን እናገራለሁና ስሙ ከንፈሮቼም ቅን ነገርን ለመናገር ይከፈታሉ። |
6 Hear; for I will speak of excellent things; and the opening of my lips shall be right things. |
7 አፌ እውነትን ይናገራልና፥ ከንፈሮቼም ክፋትን ይጸየፋሉ። |
7 For my mouth shall speak truth; and wickedness is an abomination to my lips. |
8 የአፌ ቃላት ሁሉ ጽድቅ ናቸው ጠማማ ዘወርዋራም አይደሉም። |
8 All the words of my mouth are in righteousness; there is nothing froward or perverse in them. |
9 እነርሱ በሚያስተውሉ ዘንድ የቀኑ ናቸው፥ እውቀትንም ካገኙአት ሰዎች ጋር የተስማሙ ናቸው። |
9 They are all plain to him that understandeth, and right to them that find knowledge. |
10 ተግሣጼን እንጂ ብርን አትቀበሉ፥ ከምዝምዝ ወርቅም ይልቅ እውቀትን ተቀበሉ። |
10 Receive my instruction, and not silver; and knowledge rather than choice gold. |
11 ጥበብ ከቀይ ዕንቍ ትበልጣለችና የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም። |
11 For wisdom is better than rubies; and all the things that may be desired are not to be compared to it. |
12 እኔ ጥበብ በብልሃት ተቀምጫለሁ፥ እውቀትንም ጥንቃቄንም አግኝቻለሁ። |
12 I wisdom dwell with prudence, and find out knowledge of witty inventions. |
13 እግዚአብሔርን መፍራት ክፋትን ይጠላል ትዕቢትንና እብሪትን ክፉንም መንገድ ጠማማውንም አፍ እጠላለሁ። |
13 The fear of the Lord is to hate evil: pride, and arrogancy, and the evil way, and the froward mouth, do I hate. |
14 ምክርና መልካም ጥበብ የእኔ ነው ማስተዋል እኔ ነኝ፥ ብርታትም አለኝ። |
14 Counsel is mine, and sound wisdom: I am understanding; I have strength. |
15 ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፥ ሹማምቶችም የቀናውን ነገር ይደነግጋሉ። |
15 By me kings reign, and princes decree justice. |
16 አለቆች በእኔ ያዝዛሉ፥ ክቡራንና የምድር ፈራጆችም ሁሉ። |
16 By me princes rule, and nobles, even all the judges of the earth. |
17 እኔ የሚወድዱኝን እወድዳለሁ፥ ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል። |
17 I love them that love me; and those that seek me early shall find me. |
18 ብልጥግናና ክብር በእኔ ዘንድ ነው፥ ብዙ ሀብትና ጽድቅም። |
18 Riches and honour are with me; yea, durable riches and righteousness. |
19 ፍሬዬም ከምዝምዝ ወርቅ ይሻላል፥ ቡቃያዬም ከተመረጠች ብር። |
19 My fruit is better than gold, yea, than fine gold; and my revenue than choice silver. |
20 እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፥ በፍርድም ጎዳና መካከል፥ |
20 I lead in the way of righteousness, in the midst of the paths of judgment: |
21 ለሚወድዱኝ ርስት አወርሳቸው ዘንድ ቤተ መዛግብታቸውንም እሞላ ዘንድ። |
21 That I may cause those that love me to inherit substance; and I will fill their treasures. |
22 እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ፥ በቀድሞ ሥራው መጀመሪያ። |
22 The Lord possessed me in the beginning of his way, before his works of old. |
23 ከጥንቱ ከዘላለም ጀምሮ ተሾምሁ ምድር ከመፈጠርዋ አስቀድሞ። |
23 I was set up from everlasting, from the beginning, or ever the earth was. |
24 ቀላያት ገና ሳይኖሩ እኔ ተወለድሁ፥ የውኃ ምንጮች ገና ሳይፈልቁ። |
24 When there were no depths, I was brought forth; when there were no fountains abounding with water. |
25 ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ፥ ከኮረብቶች በፊት እኔ ተወለድሁ፥ |
25 Before the mountains were settled, before the hills was I brought forth: |
26 ምድሪቱንና ሜዳውን ገና ሳይፈጥር የመጀመሪያውን የዓለም አፈር። |
26 While as yet he had not made the earth, nor the fields, nor the highest part of the dust of the world. |
27 ሰማዮችን በዘረጋ ጊዜ አብሬ ነበርሁ፥ በቀላያት ፊት ክበብን በደነገገ ጊዜ፥ |
27 When he prepared the heavens, I was there: when he set a compass upon the face of the depth: |
28 ደመናትን በላይ ባዘጋጀ ጊዜ፥ የቀላይን ምንጮች ባጸና ጊዜ፥ |
28 When he established the clouds above: when he strengthened the fountains of the deep: |
29 ለባሕርም ዳርቻን በወሰነ ጊዜ ውኃ ከትእዛዙ እንዳያልፍ፥ የምድርን መሠረት በመሠረተ ጊዜ፥ |
29 When he gave to the sea his decree, that the waters should not pass his commandment: when he appointed the foundations of the earth: |
30 የዚያን ጊዜ እኔ በእርሱ ዘንድ ዋና ሠራተኛ ነበርሁ ዕለት ዕለት ደስ አሰኘው ነበርሁ፥ በፊቱም ሁልጊዜ ደስ ይለኝ ነበርሁ፥ |
30 Then I was by him, as one brought up with him: and I was daily his delight, rejoicing always before him; |
31 ደስታዬም በምድሩ ተድላዬም በሰው ልጆች ነበረ። |
31 Rejoicing in the habitable part of his earth; and my delights were with the sons of men. |
32 አሁንም ልጆቼ ሆይ፥ ስሙኝ መንገዴንም የሚጠብቁ ምስጉኖች ናቸው። |
32 Now therefore hearken unto me, O ye children: for blessed are they that keep my ways. |
33 ትምህርቴን ስሙ፥ ጠቢባንም ሁኑ፥ ቸል አትበሉትም። |
33 Hear instruction, and be wise, and refuse it not. |
34 የሚሰማኝ ሰው ምስጉን ነው ዕለት ዕለት በቤቴ መግቢያ የሚተጋ፥ የደጄንም መድረክ የሚጠብቅ። |
34 Blessed is the man that heareth me, watching daily at my gates, waiting at the posts of my doors. |
35 እኔን ያገኘ ሕይወትን ያገኛልና። ከእግዚአብሔርም ሞገስን ያገኛልና። |
35 For whoso findeth me findeth life, and shall obtain favour of the Lord. |
36 እኔን ያጣ ግን ራሱን ይጐዳል የሚጠሉኝ ሁሉ ሞትን ይወድዳሉ። |
36 But he that sinneth against me wrongeth his own soul: all they that hate me love death. |