መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #104
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 104 |
Psalm 104 |
1 ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ አንተ እጅግ ታላቅ ነህ ክብርንና ግርማን ለበስህ። |
1 Bless the Lord, O my soul. O Lord my God, thou art very great; thou art clothed with honour and majesty. |
2 ብርሃንን እንደ ልብስ ለበስህ ሰማይንም እንደ መጋረጃ ዘረጋህ |
2 Who coverest thyself with light as with a garment: who stretchest out the heavens like a curtain: |
3 እልፍኙን በውኃ የሚሠራ፥ ሰረገላውን ደመና የሚያደርግ፥ በነፋስ ክንፍም የሚሄድ፥ |
3 Who layeth the beams of his chambers in the waters: who maketh the clouds his chariot: who walketh upon the wings of the wind: |
4 መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል። |
4 Who maketh his angels spirits; his ministers a flaming fire: |
5 ለዘላለም እንዳትናወጥ ምድርን በመሠረትዋ ላይ መሠረታት። |
5 Who laid the foundations of the earth, that it should not be removed for ever. |
6 በጥልቅ እንደ ልብስ ከደንሃት፥ በተራሮችም ላይ ውኆች ይቆማሉ። |
6 Thou coveredst it with the deep as with a garment: the waters stood above the mountains. |
7 ከዘለፋህም ይሸሻሉ፥ ከነጐድጓድህም ድምፅ ይደነግጣሉ |
7 At thy rebuke they fled; at the voice of thy thunder they hasted away. |
8 ወደ ተራሮች ይወጣሉ፥ ወደ ቈላዎች ወዳዘጋጀህላቸው ስፍራ ይወርዳሉ |
8 They go up by the mountains; they go down by the valleys unto the place which thou hast founded for them. |
9 እንዳያልፉትም ድንበር አደረግህላቸው ምድርን ይከድኑ ዘንድ እንዳይመለሱ። |
9 Thou hast set a bound that they may not pass over; that they turn not again to cover the earth. |
10 ምንጮችን ወደ ቈላዎች ይልካል በተራሮች መካከል ውኆች ያልፋሉ |
10 He sendeth the springs into the valleys, which run among the hills. |
11 የዱር አራዊትን ሁሉ ያጠጣሉ፥ የበረሃ አህያዎችም ጥማታቸውን ይረካሉ። |
11 They give drink to every beast of the field: the wild asses quench their thirst. |
12 የሰማይም ወፎች በእነርሱ ዘንድ ያድራሉ፥ በድንጋዩ ስንጥቅ መካከልም ይጮኻሉ። |
12 By them shall the fowls of the heaven have their habitation, which sing among the branches. |
13 ተራሮችን ከላይ የሚያጠጣቸው ከሥራህ ፍሬ ምድር ትጠግባለች። |
13 He watereth the hills from his chambers: the earth is satisfied with the fruit of thy works. |
14 እንጀራን ከምድር ያወጣ ዘንድ ለምለሙን ለሰው ልጆች ጥቅም፥ ሣርንም ለእንስሳ ያበቅላል። |
14 He causeth the grass to grow for the cattle, and herb for the service of man: that he may bring forth food out of the earth; |
15 ወይን የሰውን ልብ ደስ ያሰኛል፥ ዘይትም ፊትን ያበራል፥ እህልም የሰውን ጕልበት ያጠነክራል። |
15 And wine that maketh glad the heart of man, and oil to make his face to shine, and bread which strengtheneth man’s heart. |
16 የእግዚአብሔር ዛፎች እርሱም የተከላቸው የሊባኖስ ዝግባዎች ይጠግባሉ። |
16 The trees of the Lord are full of sap; the cedars of Lebanon, which he hath planted; |
17 በዚያም ወፎች ይዋለዳሉ፥ የሽመላ ቤትም የእነርሱ ጎረቤት ነው። |
17 Where the birds make their nests: as for the stork, the fir trees are her house. |
18 ረጃጅም ተራራዎች ለዋላዎች፥ ድንጋዮችም ለእሽኮኮች መሸሻ ናቸው። |
18 The high hills are a refuge for the wild goats; and the rocks for the conies. |
19 ጨረቃን ለጊዜዎች አደረገ ፀሐይም መግቢያውን ያውቃል። |
19 He appointed the moon for seasons: the sun knoweth his going down. |
20 ጨለማ ታደርጋለህ ሌሊትም ይሆናል በእርሱም የዱር አራዊት ሁሉ ይወጡበታል። |
20 Thou makest darkness, and it is night: wherein all the beasts of the forest do creep forth. |
21 የአንበሳ ግልገሎች ለመንጠቅ ይጮኻሉ፥ ከእግዚአብሔርም ምግባቸውን ይሻሉ። |
21 The young lions roar after their prey, and seek their meat from God. |
22 ፀሐይ ስትወጣ ይሰበሰባሉ በየዋሻቸውም ይተኛሉ። |
22 The sun ariseth, they gather themselves together, and lay them down in their dens. |
23 ሰው ወደ ተግባሩ፥ እስኪመሽም ድረስ ወደ ሥራው ይወጣል። |
23 Man goeth forth unto his work and to his labour until the evening. |
24 አቤቱ፥ ሥራህ እጅግ ብዙ ነው ሁሉን በጥበብ አደረግህ፥ ምድርም ከፍጥረትህ ተሞላች። |
24 O Lord, how manifold are thy works! in wisdom hast thou made them all: the earth is full of thy riches. |
25 ይህች ባሕር ታላቅና ሰፊ ናት በዚያ ስፍራ ቍጥር የሌለው ተንቀሳቃሽ፥ ታላላቆችና ታናናሾች እንስሶች አሉ። |
25 So is this great and wide sea, wherein are things creeping innumerable, both small and great beasts. |
26 በዚያ ጊዜ መርከቦች ይሄዳሉ፥ በዚያም ላይ የፈጠርኸው ዘንዶ ይጫወትበታል። |
26 There go the ships: there is that leviathan, whom thou hast made to play therein. |
27 ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸው ዘንድ እነዚህ ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ። |
27 These wait all upon thee; that thou mayest give them their meat in due season. |
28 በሰጠሃቸውም ጊዜ ይሰበስባሉ እጅህን ትከፍታለህ፥ ከመልካም ነገርም ይጠግባሉ። |
28 That thou givest them they gather: thou openest thine hand, they are filled with good. |
29 ፊትህን ስትሰውር ይደነግጣሉ ነፍሳቸውን ታወጣለህ ይሞታሉም፥ ወደ አፈራቸውም ይመለሳሉ። |
29 Thou hidest thy face, they are troubled: thou takest away their breath, they die, and return to their dust. |
30 መንፈስህን ትልካለህ ይፈጠራሉም፥ የምድርንም ፊት ታድሳለህ። |
30 Thou sendest forth thy spirit, they are created: and thou renewest the face of the earth. |
31 የእግዚአብሔር ክብር ለዘላለም ይሁን እግዚአብሔር በሥራው ደስ ይለዋል። |
31 The glory of the Lord shall endure for ever: the Lord shall rejoice in his works. |
32 ምድርን ያያል እንድትንቀጠቀጥም ያደርጋል ተራሮችን ይዳስሳል ይጤሳሉም። |
32 He looketh on the earth, and it trembleth: he toucheth the hills, and they smoke. |
33 በሕይወቴ ሳለሁ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ፥ ለአምላኬም በምኖርበት ዘመን ሁሉ እዘምራለሁ። |
33 I will sing unto the Lord as long as I live: I will sing praise to my God while I have my being. |
34 ቃሌ ለእርሱ ይጣፍጠው፥ እኔም በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል። |
34 My meditation of him shall be sweet: I will be glad in the Lord. |
35 ኅጥኣን ከምድር ይጥፉ ዓመፀኞች እንግዲህ አይገኙ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ። ሃሌ ሉያ። |
35 Let the sinners be consumed out of the earth, and let the wicked be no more. Bless thou the Lord, O my soul. Praise ye the Lord. |