መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #29
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 29

Psalm 29

1 የአምላክ ልጆች ሆይ፥ ለእግዚአብሔር አምጡ። ክብርንና ምስጋናን ለእግዚአብሔር አምጡ።

1 Give unto the Lord, O ye mighty, give unto the Lord glory and strength.

2 የስሙን ክብር ለእግዚአብሔር አምጡ፥ በቅድስናው ስፍራ ለእግዚአብሔር ስገዱ።

2 Give unto the Lord the glory due unto his name; worship the Lord in the beauty of holiness.

3 የእግዚአብሔር ድምፅ በውኆች ላይ፥ የክብር አምላክ አንጐደጐደ፥ እግዚአብሔር በብዙ ውኆች ላይ።

3 The voice of the Lord is upon the waters: the God of glory thundereth: the Lord is upon many waters.

4 የእግዚአብሔር ድምፅ በኃይል ነው የእግዚአብሔር ድምፅ በታላቅ ክብር ነው።

4 The voice of the Lord is powerful; the voice of the Lord is full of majesty.

5 የእግዚአብር ድምፅ ዝግባን ይሰብራል እግዚአብሔር የሊባኖስን ዝግባ ይቀጠቅጣል።

5 The voice of the Lord breaketh the cedars; yea, the Lord breaketh the cedars of Lebanon.

6 እንደ ጥጃ ሊባኖስን፥ አንድ ቀን እንዳለው አውሬ ልጅ ስርዮንን ያዘልላቸዋል።

6 He maketh them also to skip like a calf; Lebanon and Sirion like a young unicorn.

7 የእግዚአብሔር ድምፅ የእሳቱን ነበልባል ይቈርጣል።

7 The voice of the Lord divideth the flames of fire.

8 የእግዚአብሔር ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፥ እግዚአብሔር የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል።

8 The voice of the Lord shaketh the wilderness; the Lord shaketh the wilderness of Kadesh.

9 የእግዚአብሔር ድምፅ ዋላዎችን ያጠነክራቸዋል፥ ጫካዎቹንም ይገልጣል ሁሉም በመቅደሱ። ምስጋና ይላል።

9 The voice of the Lord maketh the hinds to calve, and discovereth the forests: and in his temple doth every one speak of his glory.

10 እግዚአብሔር የጥፋት ውኃን ሰብስቦአል እግዚአብሔር ለዘላለም ንጉሥ ሆኖ ይቀመጣል።

10 The Lord sitteth upon the flood; yea, the Lord sitteth King for ever.

11 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ኃይልን ይሰጣል እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።

11 The Lord will give strength unto his people; the Lord will bless his people with peace.