መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #32
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 32

Ps 32

1 መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው።

1 Blessed is he whose transgression is forgiven, whose sin is covered.

2 እግዚአብሔር በደልን የማይቈጥርበት በመንፈሱም ሽንገላ የሌለበት ሰው ምስጉን ነው።

2 Blessed is the man unto whom the Lord imputeth not iniquity, and in whose spirit there is no guile.

3 ሁልጊዜ ከመጮኼ የተነሣ ዝም ባልሁ ጊዜ አጥንቶቼ ተበላሹ

3 When I kept silence, my bones waxed old through my roaring all the day long.

4 በቀንና በሌሊት እጅህ ከብዳብኛለችና፥ እርጥበቴም ለበጋ ትኵሳት ተለወጠ።

4 For day and night thy hand was heavy upon me: my moisture is turned into the drought of summer. Selah.

5 ኃጢአቴን ለአንተ አስታወቅሁ፥ በደሌንም አልሸፈንሁም ለእግዚአብሔር መተላለፌን እነግራለሁ አልሁ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውህልኝ።

5 I acknowledged my sin unto thee, and mine iniquity have I not hid. I said, I will confess my transgressions unto the Lord; and thou forgavest the iniquity of my sin. Selah.

6 ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል ብዙ የጥፋት ውኃም ወደ እርሱ አይቀርብም።

6 For this shall every one that is godly pray unto thee in a time when thou mayest be found: surely in the floods of great waters they shall not come nigh unto him.

7 አንተ ለእኔ መሸሸጊያዬ ነህ፥ ከጣርም ትጠብቀኛለህ ከከበቡኝ ታድነኝ ዘንድ ደስታዬ ነህ።

7 Thou art my hiding place; thou shalt preserve me from trouble; thou shalt compass me about with songs of deliverance. Selah.

8 አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።

8 I will instruct thee and teach thee in the way which thou shalt go: I will guide thee with mine eye.

9 ወደ አንተ እንዳይቀርቡ በልባብና በልጓም ጉንጫቸውን እንደሚለጕሙአቸው፥ ልብ እንደሌላቸው እንደ ፈረስና እንደ በቅሎ አትሁኑ።

9 Be ye not as the horse, or as the mule, which have no understanding: whose mouth must be held in with bit and bridle, lest they come near unto thee.

10 በኃጢአተኛ ብዙ መቅሠፍት አለበት በእግዚአብሔር የሚታመነውን ግን ምሕረት ይከብበዋል።

10 Many sorrows shall be to the wicked: but he that trusteth in the Lord, mercy shall compass him about.

11 ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ሐሤትም አድርጉ

11 Be glad in the Lord, and rejoice, ye righteous: and shout for joy, all ye that are upright in heart.