መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #33
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 33

Psalm 33

1 ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ለቅኖች ምስጋና ይገባል።

1 Rejoice in the Lord, O ye righteous: for praise is comely for the upright.

2 እግዚአብሔርን በመሰንቆ አመስግኑት፥ አሥር አውታርም ባለው በበገና ዘምሩለት።

2 Praise the Lord with harp: sing unto him with the psaltery and an instrument of ten strings.

3 አዲስ ቅኔም ተቀኙለት፥ በእልልታም መልካም ዝማሬ ዘምሩ

3 Sing unto him a new song; play skilfully with a loud noise.

4 የእግዚአብሔር ቃል ቅን ነውና ሥራውም ሁሉ በእምነት ነውና።

4 For the word of the Lord is right; and all his works are done in truth.

5 ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።

5 He loveth righteousness and judgment: the earth is full of the goodness of the Lord.

6 በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ

6 By the word of the Lord were the heavens made; and all the host of them by the breath of his mouth.

7 የባሕርን ውኃ እንደ ረዋት የሚሰበስበው፥ ቀላዮችንም በመዝገቦች የሚያኖራቸው።

7 He gathereth the waters of the sea together as an heap: he layeth up the depth in storehouses.

8 ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን ትፍራው፥ በዓለም የሚኖሩ ሁሉም ከእርሱ የተነሣ ይደንግጡ።

8 Let all the earth fear the Lord: let all the inhabitants of the world stand in awe of him.

9 እርሱ ተናግሮአልና፥ ሆኑም እርሱ አዘዘ፥ ጸኑም።

9 For he spake, and it was done; he commanded, and it stood fast.

10 እግዚአብሔር የአሕዛብን ምክር ያጠፋል፥ የአሕዛብንም አሳብ ይመልሳል።

10 The Lord bringeth the counsel of the heathen to nought: he maketh the devices of the people of none effect.

11 የእግዚአብሔር ምክር ግን ለዘላለም ይኖራል። የልቡም አሳብ ለልጅ ልጅ ነው።

11 The counsel of the Lord standeth for ever, the thoughts of his heart to all generations.

12 እግዚአብሔር አምላኩ የሚሆንለት ሕዝብ ምስጉን ነው፥ እርሱ ለርስቱ የመረጠው ሕዝብ።

12 Blessed is the nation whose God is the Lord; and the people whom he hath chosen for his own inheritance.

13 እግዚአብሔር ከሰማይ ተመለከተ፥ የሰውንም ልጆች ሁሉ አየ።

13 The Lord looketh from heaven; he beholdeth all the sons of men.

14 ከማደሪያው ቦታ ሆኖ በምድር ወደሚኖሩ ሁሉ ተመለከተ፥

14 From the place of his habitation he looketh upon all the inhabitants of the earth.

15 እርሱ ብቻውን ልባቸውን የሠራ ሥራቸውንም ሁሉ የሚያስተውል።

15 He fashioneth their hearts alike; he considereth all their works.

16 ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም።

16 There is no king saved by the multitude of an host: a mighty man is not delivered by much strength.

17 ፈረስም ከንቱ ነው፥ አያድንም በኃይሉም ብዛት አያመልጥም።

17 An horse is a vain thing for safety: neither shall he deliver any by his great strength.

18 እነሆ፥ የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደሚፈሩት ናቸው፥ በምሕረቱም ወደሚታመኑ፥

18 Behold, the eye of the Lord is upon them that fear him, upon them that hope in his mercy;

19 ነፍሳቸውን ከሞት ያድን ዘንድ፥ በራብም ጊዜ ይመግባቸው ዘንድ።

19 To deliver their soul from death, and to keep them alive in famine.

20 ነፍሳችን እግዚአብሔርን ተስፋ ታደርገዋለች፥ ረዳታችንና መጠጊያችን እርሱ ነውና።

20 Our soul waiteth for the Lord: he is our help and our shield.

21 ልባችን በእርሱ ደስ ይለዋልና፥ በቅዱስ ስሙም ታምነናልና።

21 For our heart shall rejoice in him, because we have trusted in his holy name.

22 አቤቱ፥ ምሕረትህ በላያችን ትሁን፥ በአንተ እንደ ታመንን።

22 Let thy mercy, O Lord, be upon us, according as we hope in thee.