መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #42
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 42

Ps 42

1 ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች።

1 As the hart panteth after the water brooks, so panteth my soul after thee, O God.

2 ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?

2 My soul thirsteth for God, for the living God: when shall I come and appear before God?

3 ዘወትር። አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ።

3 My tears have been my meat day and night, while they continually say unto me, Where is thy God?

4 ይህን ሳስብ ነፍሴ በእኔ ውስጥ ፈሰሰች፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።

4 When I remember these things, I pour out my soul in me: for I had gone with the multitude, I went with them to the house of God, with the voice of joy and praise, with a multitude that kept holyday.

5 ነፍሴ ሆይ፥ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ ታውኪኛለሽ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ።

5 Why art thou cast down, O my soul? and why art thou disquieted in me? hope thou in God: for I shall yet praise him for the help of his countenance.

6 አምላኬ ሆይ፥ ነፍሴ በእኔ ውስጥ ታወከች ስለዚህ በዮርዳኖስ ምድር በአርሞንኤምም በታናሹ ተራራ አስብሃለሁ።

6 O my God, my soul is cast down within me: therefore will I remember thee from the land of Jordan, and of the Hermonites, from the hill Mizar.

7 በፍዋፍዋቴህ ድምፅ ቀላይ ቀላይን ትጠራታለች ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፈ።

7 Deep calleth unto deep at the noise of thy waterspouts: all thy waves and thy billows are gone over me.

8 እግዚአብሔር በቀን ቸርነቱን ያዝዛል፥ በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ ይሆናል የእኔ ስእለት ለሕይወቴ አምላክ ነው።

8 Yet the Lord will command his lovingkindness in the daytime, and in the night his song shall be with me, and my prayer unto the God of my life.

9 እግዚአብሔርን፦ አንተ መጠጊያዬ ነህ ለምን ረሳኸኝ? ጠላቶቼ ሲያስጨንቁኝ ለምን አዝኜ እመላለሳለሁ? እለዋለሁ።

9 I will say unto God my rock, Why hast thou forgotten me? why go I mourning because of the oppression of the enemy?

10 ጠላቶቼ ሁልጊዜ። አምላክህ ወዴት ነው? ባሉኝ ጊዜ አጥንቶቼን እየቀለጣጠሙ ሰደቡኝ።

10 As with a sword in my bones, mine enemies reproach me; while they say daily unto me, Where is thy God?

11 ነፍሴ ሆይ፥ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ ታውኪኛለሽ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ።

11 Why art thou cast down, O my soul? and why art thou disquieted within me? hope thou in God: for I shall yet praise him, who is the health of my countenance, and my God.