መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #119 Verse 1-176
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 119 Verse 1-88 |
Ps 119 Verse 1-88 |
1 በመንገዳቸው ንጹሐን የሆኑ፥ በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ ምስጉኖች ናቸው። |
1 ALEPH.Blessed are the undefiled in the way, who walk in the law of the Lord. |
2 ምስክሩን የሚፈልጉ፥ በፍጹም ልብ የሚሹት ምስጉኖች ናቸው |
2 Blessed are they that keep his testimonies, and that seek him with the whole heart. |
3 ዓመፅንም አያደርጉም፥ በመንገዶቹም ይሄዳሉ። |
3 They also do no iniquity: they walk in his ways. |
4 ትእዛዛትህን እጅግ እንጠብቅ ዘንድ አንተ አዘዝህ። |
4 Thou hast commanded us to keep thy precepts diligently. |
5 ሥርዓትህን ለመጠበቅ መንገዶቼ ይቀኑ ዘንድ እወድድ ነበር። |
5 O that my ways were directed to keep thy statutes! |
6 ትእዛዝህን ሁሉ ስመለከት በዚያን ጊዜ አላፍርም። |
6 Then shall I not be ashamed, when I have respect unto all thy commandments. |
7 አቤቱ፥ የጽድቅህን ፍርድ ስማር በቅን ልብ አመሰግንሃለሁ። |
7 I will praise thee with uprightness of heart, when I shall have learned thy righteous judgments. |
8 ሥርዓትህን እጠብቃለሁ በፍጹም አትጣለኝ። |
8 I will keep thy statutes: O forsake me not utterly. |
9 ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው። |
9 BETH.Wherewithal shall a young man cleanse his way? by taking heed thereto according to thy word. |
10 በፍጹም ልቤ ፈለግሁህ፥ ከትእዛዝህ አታርቀኝ። |
10 With my whole heart have I sought thee: O let me not wander from thy commandments. |
11 አንተን እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ። |
11 Thy word have I hid in mine heart, that I might not sin against thee. |
12 አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ ሥርዓትህን አስተምረኝ። |
12 Blessed art thou, O Lord: teach me thy statutes. |
13 የአፍህን ፍርድ ሁሉ በከንፈሬ ነገርሁ። |
13 With my lips have I declared all the judgments of thy mouth. |
14 እንደ ብልጥግና ሁሉ በምስክርህ መንገድ ደስ አለኝ። |
14 I have rejoiced in the way of thy testimonies, as much as in all riches. |
15 ትእዛዝህን አሰላስላለሁ፥ መንገድህንም እፈልጋለሁ። |
15 I will meditate in thy precepts, and have respect unto thy ways. |
16 በትእዛዝህ ደስ ይለኛል ቃልህንም አልረሳም። |
16 I will delight myself in thy statutes: I will not forget thy word. |
17 ለባሪያህ መልካም አድርግ ሕያው እንድሆን፥ ቃልህንም እንድጠብቅ። |
17 GIMEL.Deal bountifully with thy servant, that I may live, and keep thy word. |
18 ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ። |
18 Open thou mine eyes, that I may behold wondrous things out of thy law. |
19 እኔ በምድር እንግዳ ነኝ ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር። |
19 I am a stranger in the earth: hide not thy commandments from me. |
20 ነፍሴ ሁልጊዜ ፍርድህን እጅግ ናፈቀች። |
20 My soul breaketh for the longing that it hath unto thy judgments at all times. |
21 ከትእዛዛትህ የሳቱትን ትዕቢተኞችንና ርጉማንን ዘለፍህ። |
21 Thou hast rebuked the proud that are cursed, which do err from thy commandments. |
22 ምስክርህን ፈልጌአለሁና። ስድብንና ነውርን ከእኔ አርቅ። |
22 Remove from me reproach and contempt; for I have kept thy testimonies. |
23 አለቆች ደግሞ ተቀምጠው እኔን አሙኝ ባሪያህ ግን ሕግህን ያሰላስል ነበር። |
23 Princes also did sit and speak against me: but thy servant did meditate in thy statutes. |
24 ምስክርህም ተድላዬ ነው፥ ሥርዓትህም መካሪዬ ነው። |
24 Thy testimonies also are my delight and my counsellors. |
25 ነፍሴ ወደ ምድር ተጠጋች እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። |
25 DALETH.My soul cleaveth unto the dust: quicken thou me according to thy word. |
26 መንገድህን ነገርሁ ሰማኸኝም ሥርዓትህን አስተምረኝ። |
26 I have declared my ways, and thou heardest me: teach me thy statutes. |
27 የሥርዓትህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ተኣምራትህንም አሰላስላለሁ። |
27 Make me to understand the way of thy precepts: so shall I talk of thy wondrous works. |
28 ከኀዘን የተነሣ ነፍሴ አንቀላፋች በቃልህ አጠንክረኝ። |
28 My soul melteth for heaviness: strengthen thou me according unto thy word. |
29 የዓመፅን መንገድ ከእኔ አርቅ፥ በሕግህም ማረኝ |
29 Remove from me the way of lying: and grant me thy law graciously. |
30 የእውነትህን መንገድ መረጥሁ፥ ፍርድህንም አልረሳሁም። |
30 I have chosen the way of truth: thy judgments have I laid before me. |
31 አቤቱ፥ ምስክርህን ተጠጋሁ አታሳፍረኝ። |
31 I have stuck unto thy testimonies: O Lord, put me not to shame. |
32 ልቤን ባሰፋኸው ጊዜ፥ በትእዛዝህ መንገድ ሮጥሁ። |
32 I will run the way of thy commandments, when thou shalt enlarge my heart. |
33 አቤቱ፥ የሥርዓትህን መንገድ አስተምረኝ፥ ሁልጊዜም እፈልገዋለሁ። |
33 HE.Teach me, O Lord, the way of thy statutes; and I shall keep it unto the end. |
34 እንዳስተውል አድርገኝ፥ ሕግህንም እፈልጋለሁ በፍጹም ልቤም እጠብቀዋለሁ። |
34 Give me understanding, and I shall keep thy law; yea, I shall observe it with my whole heart. |
35 እርስዋን ወድጃለሁና የትእዛዝህን መንገድ ምራኝ። |
35 Make me to go in the path of thy commandments; for therein do I delight. |
36 ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን። |
36 Incline my heart unto thy testimonies, and not to covetousness. |
37 ከንቱ ነገርን እንዳያዩ ዓይኖቼን መልስ በመንገድህ ሕያው አድርገኝ። |
37 Turn away mine eyes from beholding vanity; and quicken thou me in thy way. |
38 እንዲፈራህ ባሪያህን በቃልህ አጽና። |
38 Stablish thy word unto thy servant, who is devoted to thy fear. |
39 ፍርድህ መልካም ናትና የተጠራጠርሁትን ስድብ ከእኔ አርቅ። |
39 Turn away my reproach which I fear: for thy judgments are good. |
40 እነሆ፥ ትእዛዝህን ናፈቅሁ በጽድቅህ ሕያው አድርገኝ |
40 Behold, I have longed after thy precepts: quicken me in thy righteousness. |
41 አቤቱ፥ እንደ ቃልህ፥ ምሕረትህና መድኃኒትህ ይምጡልኝ። |
41 VAU.Let thy mercies come also unto me, O Lord, even thy salvation, according to thy word. |
42 በቃልህ ታምኛለሁና ለሚሰድቡኝ በነገር እመልስላቸዋለሁ። |
42 So shall I have wherewith to answer him that reproacheth me: for I trust in thy word. |
43 በፍርድህም ታምኛለሁና የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ። |
43 And take not the word of truth utterly out of my mouth; for I have hoped in thy judgments. |
44 ለዘላለም ዓለም ሁልጊዜ ሕግህን እጠብቃለሁ። |
44 So shall I keep thy law continually for ever and ever. |
45 ትእዛዛትህንም ፈልጌአለሁና አስፍቼ እሄዳለሁ። |
45 And I will walk at liberty: for I seek thy precepts. |
46 በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም |
46 I will speak of thy testimonies also before kings, and will not be ashamed. |
47 እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል። |
47 And I will delight myself in thy commandments, which I have loved. |
48 እጆቼንም ወደ ወደድኋቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ። |
48 My hands also will I lift up unto thy commandments, which I have loved; and I will meditate in thy statutes. |
49 ለባሪያህ ተስፋ ያስደረግኸውን ቃልህን አስብ። |
49 ZAIN.Remember the word unto thy servant, upon which thou hast caused me to hope. |
50 ቃልህ ሕያው አድርጎኛልና ይህች በመከራዬ ደስ አሰኘችኝ። |
50 This is my comfort in my affliction: for thy word hath quickened me. |
51 ትዕቢተኞች እጅግ ዐመፁ እኔ ግን ከሕግህ አልራቅሁም። |
51 The proud have had me greatly in derision: yet have I not declined from thy law. |
52 ከጥንት የነበረውን ፍርድህን አሰብሁ፥ አቤቱ፥ ተጽናናሁም። |
52 I remembered thy judgments of old, O Lord; and have comforted myself. |
53 ሕግህን ከተዉ ከኃጢአተኞች የተነሣ ኅዘን ያዘኝ። |
53 Horror hath taken hold upon me because of the wicked that forsake thy law. |
54 በእንግድነቴ አገር ሥርዓትህ መዝሙር ሆነችኝ። |
54 Thy statutes have been my songs in the house of my pilgrimage. |
55 አቤቱ፥ በሌሊት ስምህን አሰብሁ፥ ሕግህንም ጠበቅሁ። |
55 I have remembered thy name, O Lord, in the night, and have kept thy law. |
56 ትእዛዛትህንም ፈልጌአለሁና ይህች ሆነችልኝ። |
56 This I had, because I kept thy precepts. |
57 እግዚአብሔር ክፍሌ ነው ሕግህን እጠብቃለሁ አልሁ። |
57 CHETH.Thou art my portion, O Lord: I have said that I would keep thy words. |
58 በፍጹም ልቤ ወደ ፊትህ ተማለልሁ እንደ ቃልህ ማረኝ። |
58 I intreated thy favour with my whole heart: be merciful unto me according to thy word. |
59 ስለ መንገዶችህ አሰብሁ፥ እግሬንም ወደ ምስክሮችህ መለስሁ። |
59 I thought on my ways, and turned my feet unto thy testimonies. |
60 ትእዛዝህን ለመጠበቅ ጨከንሁ አልዘገየሁምም። |
60 I made haste, and delayed not to keep thy commandments. |
61 የኃጥኣን ገመዶች ተተበተቡብኝ ሕግህን ግን አልረሳሁም። |
61 The bands of the wicked have robbed me: but I have not forgotten thy law. |
62 ስለ ጽድቅህ ፍርድ፥ በእኩለ ሌሊት አመሰግንህ ዘንድ እነሣለሁ። |
62 At midnight I will rise to give thanks unto thee because of thy righteous judgments. |
63 እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፥ ትእዛዝህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ። |
63 I am a companion of all them that fear thee, and of them that keep thy precepts. |
64 አቤቱ፥ ምሕረትህ በምድር ሁሉ ሞላች ሥርዓትህን አስተምረኝ። |
64 The earth, O Lord, is full of thy mercy: teach me thy statutes. |
65 አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ለባሪያህ መልካም አደረግህ። |
65 TETH.Thou hast dealt well with thy servant, O Lord, according unto thy word. |
66 በትእዛዛትህ ታምኛለሁና መልካም ምክርና እውቀትን አስተምረኝ። |
66 Teach me good judgment and knowledge: for I have believed thy commandments. |
67 እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ። |
67 Before I was afflicted I went astray: but now have I kept thy word. |
68 አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥ በቸርነትህም ሥርዓትህን አስተምረኝ። |
68 Thou art good, and doest good; teach me thy statutes. |
69 የትዕቢተኞች ዓመፅ በላዬ በዛ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ። |
69 The proud have forged a lie against me: but I will keep thy precepts with my whole heart. |
70 ልባቸው እንደ ወተት ረጋ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል። |
70 Their heart is as fat as grease; but I delight in thy law. |
71 ሥርዓትህን እማር ዘንድ ያስጨነቅኸኝ መልካም ሆነልኝ። |
71 It is good for me that I have been afflicted; that I might learn thy statutes. |
72 ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል። |
72 The law of thy mouth is better unto me than thousands of gold and silver. |
73 እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም እንዳስተውል አድርገኝ፥ ትእዛዛትህንም እማራለሁ። |
73 JOD.Thy hands have made me and fashioned me: give me understanding, that I may learn thy commandments. |
74 በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል። |
74 They that fear thee will be glad when they see me; because I have hoped in thy word. |
75 አቤቱ፥ ፍርድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥ በእውነትህም እንዳስቸገርኸኝ አወቅሁ። |
75 I know, O Lord, that thy judgments are right, and that thou in faithfulness hast afflicted me. |
76 ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው። |
76 Let, I pray thee, thy merciful kindness be for my comfort, according to thy word unto thy servant. |
77 ሕግህ ተድላዬ ናትና ቸርነትህ ትምጣልኝ፥ በሕይወትም ልኑር። |
77 Let thy tender mercies come unto me, that I may live: for thy law is my delight. |
78 ትዕቢተኞች በዓመፅ ጠምመውብኛልና ይፈሩ እኔ ግን በትእዛዝህ እጫወታለሁ። |
78 Let the proud be ashamed; for they dealt perversely with me without a cause: but I will meditate in thy precepts. |
79 የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ። |
79 Let those that fear thee turn unto me, and those that have known thy testimonies. |
80 እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን። |
80 Let my heart be sound in thy statutes; that I be not ashamed. |
81 ነፍሴ መድኃኒትህን ናፈቀች በቃልህም ታመንሁ። |
81 CAPH.My soul fainteth for thy salvation: but I hope in thy word. |
82 መቼ ታጽናናኛለህ እያልሁ ዓይኖቼ ስለ ቃልህ ፈዘዙ። |
82 Mine eyes fail for thy word, saying, When wilt thou comfort me? |
83 በጢስ እንዳለ አቁማዳ ሆኛለሁና ሥርዓትህን ግን አልረሳሁም። |
83 For I am become like a bottle in the smoke; yet do I not forget thy statutes. |
84 የባሪያህ ዘመኖች ስንት ናቸው? በሚያሳድዱኝስ ላይ መቼ ትፈርድልኛለህ? |
84 How many are the days of thy servant? when wilt thou execute judgment on them that persecute me? |
85 ኃጢአተኞች ጨዋታን ነገሩኝ፥ አቤቱ፥ እንደ ሕግህ ግን አይደለም። |
85 The proud have digged pits for me, which are not after thy law. |
86 ትእዛዛትህ ሁሉ እውነት ናቸው በዓመፅ አሳድደውኛል እርዳኝ። |
86 All thy commandments are faithful: they persecute me wrongfully; help thou me. |
87 ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም። |
87 They had almost consumed me upon earth; but I forsook not thy precepts. |
88 እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ የአፍህንም ምስክር እጠብቃለሁ። |
88 Quicken me after thy lovingkindness; so shall I keep the testimony of thy mouth. |
89 አቤቱ፥ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል። |
89 LAMED.For ever, O Lord, thy word is settled in heaven. |
90 እውነትህ ለልጅ ልጅ ናት ምድርን መሠረትሃት እርስዋም ትኖራለች። |
90 Thy faithfulness is unto all generations: thou hast established the earth, and it abideth. |
91 ሁሉም ባሪያዎችህ ናቸውና ቀኑ በትእዛዝህ ይኖራል። |
91 They continue this day according to thine ordinances: for all are thy servants. |
92 ሕግህ ተድላዬ ባይሆን፥ ቀድሞ በጐስቍልናዬ በጠፋሁ ነበር። |
92 Unless thy law had been my delights, I should then have perished in mine affliction. |
93 በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም። |
93 I will never forget thy precepts: for with them thou hast quickened me. |
94 እኔ የአንተ ነኝ ፍርድህን ፈልጌአልሁና አድነኝ። |
94 I am thine, save me; for I have sought thy precepts. |
95 ኃጢአተኞች ያጠፉኝ ዘንድ ጠበቁኝ ምስክርህን ግን መረመርሁ። |
95 The wicked have waited for me to destroy me: but I will consider thy testimonies. |
96 የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው። |
96 I have seen an end of all perfection: but thy commandment is exceeding broad. |
97 አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው። |
97 MEM.O how love I thy law! it is my meditation all the day. |
98 ለዘላለም ለእኔ ነውና ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ። |
98 Thou through thy commandments hast made me wiser than mine enemies: for they are ever with me. |
99 ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ። |
99 I have more understanding than all my teachers: for thy testimonies are my meditation. |
100 ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ። |
100 I understand more than the ancients, because I keep thy precepts. |
101 ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ። |
101 I have refrained my feet from every evil way, that I might keep thy word. |
102 አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም። |
102 I have not departed from thy judgments: for thou hast taught me. |
103 ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ። |
103 How sweet are thy words unto my taste! yea, sweeter than honey to my mouth! |
104 ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። |
104 Through thy precepts I get understanding: therefore I hate every false way. |
105 ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው። |
105 NUN.Thy word is a lamp unto my feet, and a light unto my path. |
106 የጽድቅህን ፍርድ እጠብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸናሁም። |
106 I have sworn, and I will perform it, that I will keep thy righteous judgments. |
107 እጅግ ተቸገርሁ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። |
107 I am afflicted very much: quicken me, O Lord, according unto thy word. |
108 አቤቱ፥ ከአፌ የሚወጣውን ቃል ውደድ፥ ፍርድህንም አስተምረኝ። |
108 Accept, I beseech thee, the freewill offerings of my mouth, O Lord, and teach me thy judgments. |
109 ነፍሴ ሁልጊዜ በእጅህ ውስጥ ናት ሕግህን ግን አልረሳሁም። |
109 My soul is continually in my hand: yet do I not forget thy law. |
110 ኃጢአተኞች ወጥመድን ዘረጉብኝ ከትእዛዝህ ግን አልሳትሁም። |
110 The wicked have laid a snare for me: yet I erred not from thy precepts. |
111 የልቤ ደስታ ነውና ምስክርህን ለዘላለም ወረስሁ። |
111 Thy testimonies have I taken as an heritage for ever: for they are the rejoicing of my heart. |
112 ለዘላለም ለፍጻሜውም ትእዛዝህን አደርግ ዘንድ ልቤን አዘነበልሁ። |
112 I have inclined mine heart to perform thy statutes alway, even unto the end. |
113 ዓመፀኞችን ጠላሁ፥ ሕግህን ግን ወደድሁ። |
113 SAMECH.I hate vain thoughts: but thy law do I love. |
114 አንተ ረዳቴና መጠጊያዬ ነህ፥ በቃልህም ተማመንሁ። |
114 Thou art my hiding place and my shield: I hope in thy word. |
115 እናንተ ኃጢአተኞች፥ ከእኔ ራቁ፥ የአምላኬንም ትእዛዝ ልፈልግ። |
115 Depart from me, ye evildoers: for I will keep the commandments of my God. |
116 እንደ ቃልህ ደግፈኝ፥ ሕያውም እሆናለሁ። ከተስፋዬም አልፈር። |
116 Uphold me according unto thy word, that I may live: and let me not be ashamed of my hope. |
117 እርዳኝ እድናለሁም፥ ሁልጊዜም ሥርዓትህን እመረምራለሁ። |
117 Hold thou me up, and I shall be safe: and I will have respect unto thy statutes continually. |
118 ምኞታቸው ዓመፃ ነውና ከሥርዓትህ የሚርቁትን ሁሉ አጐሳቈልሃቸው። |
118 Thou hast trodden down all them that err from thy statutes: for their deceit is falsehood. |
119 የምድርን ኃጢአተኞች ሁሉ እንደ ርኵሰት አጠፋሃቸው ስለዚህ ምስክርህን ወደድሁ። |
119 Thou puttest away all the wicked of the earth like dross: therefore I love thy testimonies. |
120 ሥጋዬ አንተን ከመፍራት የተነሣ ደንገጠ ከፍርድህ የተነሣ ፈርቻለሁ። |
120 My flesh trembleth for fear of thee; and I am afraid of thy judgments. |
121 ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ። |
121 AIN.I have done judgment and justice: leave me not to mine oppressors. |
122 ባሪያህን በመልካም ጠብቀው ትዕቢተኞችም አይጋፉኝ። |
122 Be surety for thy servant for good: let not the proud oppress me. |
123 ዓይኖቼ ለማዳንህ፥ ለጽድቅህም ቃል ፈዘዙ። |
123 Mine eyes fail for thy salvation, and for the word of thy righteousness. |
124 ለባሪያህ እንደ ምሕረትህ አድርግ፥ ሥርዓትህንም አስተምረኝ። |
124 Deal with thy servant according unto thy mercy, and teach me thy statutes. |
125 እኔ ባሪያህ ነኝ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ምስክርህንም አውቃለሁ። |
125 I am thy servant; give me understanding, that I may know thy testimonies. |
126 ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ ነው፥ ሕግህንም ሻሩት። |
126 It is time for thee, Lord, to work: for they have made void thy law. |
127 ስለዚህ ከወርቅና ከዕንቍ ይልቅ ትእዛዝህን ወደድሁ። |
127 Therefore I love thy commandments above gold; yea, above fine gold. |
128 ስለዚህ ወደ ትእዛዝህ ሁሉ አቀናሁ፥ የዓመፅንም መንገድ ሁሉ ጠላሁ። |
128 Therefore I esteem all thy precepts concerning all things to be right; and I hate every false way. |
129 ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው። |
129 PE.Thy testimonies are wonderful: therefore doth my soul keep them. |
130 የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል። |
130 The entrance of thy words giveth light; it giveth understanding unto the simple. |
131 አፌን ከፈትሁ፥ አለከለክሁም ወደ ትእዛዝህ ናፍቄአለሁና። |
131 I opened my mouth, and panted: for I longed for thy commandments. |
132 ስምህን ለሚወድዱ እንድምታደርገው ፍርድ፥ ወደ እኔ ተመልከተ ማረኝም። |
132 Look thou upon me, and be merciful unto me, as thou usest to do unto those that love thy name. |
133 አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ። |
133 Order my steps in thy word: and let not any iniquity have dominion over me. |
134 ከሰው ግፍ አድነኝ ትእዛዝህንም እጠብቃለሁ። |
134 Deliver me from the oppression of man: so will I keep thy precepts. |
135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፥ ሥርዓትህንም አሰተምረኝ። |
135 Make thy face to shine upon thy servant; and teach me thy statutes. |
136 ሕግህን አልጠበቅሁምና የውኃ ፈሳሽ ከዓይኖቼ ፈሰሰ። |
136 Rivers of waters run down mine eyes, because they keep not thy law. |
137 አቤቱ፥ አንተ ጻድቅ ነህ፥ ፍርድህም ቅን ነው። |
137 TZADDI.Righteous art thou, O Lord, and upright are thy judgments. |
138 ምስክርህን በጽድቅ አዘዝህ፥ እጅግም ቅን ነው። |
138 Thy testimonies that thou hast commanded are righteous and very faithful. |
139 ጠላቶቼ ቃልህን ረስተዋልና የቤትህ ቅንዓት አቀለጠኝ። |
139 My zeal hath consumed me, because mine enemies have forgotten thy words. |
140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፥ ባሪያህም ወደደው። |
140 Thy word is very pure: therefore thy servant loveth it. |
141 እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ ትእዛዛትህን ግን አልረሳሁም። |
141 I am small and despised: yet do not I forget thy precepts. |
142 ጽድቅህ የዘላለም ጽድቅ ነው፥ ቃልህም እውነት ነው። |
142 Thy righteousness is an everlasting righteousness, and thy law is the truth. |
143 መከራና ችግር አገኙኝ ትእዛዛትህ ግን ተድላዬ ናቸው። |
143 Trouble and anguish have taken hold on me: yet thy commandments are my delights. |
144 ምስክርህ ለዘላለም ጽድቅ ነው እንዳስተውል አድርገኝ፥ በሕይወትም አኑረኝ። |
144 The righteousness of thy testimonies is everlasting: give me understanding, and I shall live. |
145 በፍጹም ልቤ ጮኽሁ፥ አቤቱ፥ ስማኝ ሥርዓትህን እፈልጋለሁ። |
145 KOPH.I cried with my whole heart; hear me, O Lord: I will keep thy statutes. |
146 ወደ አንተ ጮኽሁ አድነኝ፥ ምስክርህንም እጠብቃለሁ። |
146 I cried unto thee; save me, and I shall keep thy testimonies. |
147 ማለዳ ጮኽሁ ቃልህንም ተስፋ አድርጌአለሁ። |
147 I prevented the dawning of the morning, and cried: I hoped in thy word. |
148 ቃልህን አስብ ዘንድ ዓይኖቼ ለመማለድ ቀደሙ። |
148 Mine eyes prevent the night watches, that I might meditate in thy word. |
149 አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ ድምፄን ስማ እንደ ፍርድህ ሕያው አድርገኝ። |
149 Hear my voice according unto thy lovingkindness: O Lord, quicken me according to thy judgment. |
150 በዓመፃ የሚያሳድዱኝ ቀረቡ፥ ከሕግህም ራቁ። |
150 They draw nigh that follow after mischief: they are far from thy law. |
151 አቤቱ፥ አንተ ቅርብ ነህ፥ መንገዶችህም ሁሉ ቅኖች ናቸው። |
151 Thou art near, O Lord; and all thy commandments are truth. |
152 ከዘላለም እንደ መሠረትኸው ከቀድሞ ጀምሮ ከምስክርህ የተነሣ አወቅሁ። |
152 Concerning thy testimonies, I have known of old that thou hast founded them for ever. |
153 ሕግህን አልረሳሁምና ችግሬን ተመልከት አድነኝም። |
153 RESH.Consider mine affliction, and deliver me: for I do not forget thy law. |
154 ፍርዴን ፍረድ አድነኝም ስለ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። |
154 Plead my cause, and deliver me: quicken me according to thy word. |
155 መድኃኒት ከኅጥኣን ሩቅ ነው፥ ሥርዓትህን አልፈለጉምና። |
155 Salvation is far from the wicked: for they seek not thy statutes. |
156 አቤቱ፥ ቸርነትህ እጅግ ብዙ ነው እንደ ፍርድህ ሕያው አድርገኝ። |
156 Great are thy tender mercies, O Lord: quicken me according to thy judgments. |
157 ያሳደዱኝና ያስጨነቁኝ ብዙዎች ናቸው ከምስክር ግን ፈቀቅ አላልሁም። |
157 Many are my persecutors and mine enemies; yet do I not decline from thy testimonies. |
158 ቃልህን አልጠበቁምና ሰነፎችን አይቼ አዘንሁ። |
158 I beheld the transgressors, and was grieved; because they kept not thy word. |
159 ትእዛዝህን እንደ ወደድሁ ተመልከት አቤቱ፥ በምሕረትህ ሕያው አድርገኝ። |
159 Consider how I love thy precepts: quicken me, O Lord, according to thy lovingkindness. |
160 የቃልህ መጀመሪያ እውነት ነው፥ የጽድቅህንም ፍርድ ሁሉ ለዘላለም ነው። |
160 Thy word is true from the beginning: and every one of thy righteous judgments endureth for ever. |
161 ገዢዎች በከንቱ አሳደዱኝ ከቃልህ የተነሣ ግን ልቤ ደነገጠብኝ። |
161 SCHIN.Princes have persecuted me without a cause: but my heart standeth in awe of thy word. |
162 ብዙ ምርኮ እንዳገኘ በቃልህ ደስ አለኝ። |
162 I rejoice at thy word, as one that findeth great spoil. |
163 ዓመፃን ጠላሁ ተጸየፍሁም ሕግን ግን ወደድሁ። |
163 I hate and abhor lying: but thy law do I love. |
164 ስለ ጽድቅህ ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ። |
164 Seven times a day do I praise thee because of thy righteous judgments. |
165 ሕግህን ለሚወድዱ ብዙ ሰላም ነው፥ ዕንቅፋትም የለባቸውም። |
165 Great peace have they which love thy law: and nothing shall offend them. |
166 አቤቱ፥ ማዳንህን ተስፋ አደርግሁ፥ ትእዛዛትህንም ጠበቅሁ። |
166 Lord, I have hoped for thy salvation, and done thy commandments. |
167 ነፍሴ ምስክርህን ጠበቀች እጅግም ወደደችው። |
167 My soul hath kept thy testimonies; and I love them exceedingly. |
168 መንገዶቼ ሁሉ በፊትህ ናቸውና ትእዛዝህንና ምስክርህን ጠበቅሁ። |
168 I have kept thy precepts and thy testimonies: for all my ways are before thee. |
169 አቤቱ፥ ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትቅረብ እንደ ቃልህም አስተዋይ አድርገኝ። |
169 TAU.Let my cry come near before thee, O Lord: give me understanding according to thy word. |
170 ልመናዬ ወደ ፊትህ ትድረስ እንደ ቃልህ አድነኝ። |
170 Let my supplication come before thee: deliver me according to thy word. |
171 ሥርዓትህን አስተምረኸኛልና ከንፈሮቼ ምስጋናን አወጡ። |
171 My lips shall utter praise, when thou hast taught me thy statutes. |
172 ትእዛዛትህ ሁሉ ጽድቅ ናቸውና አንደበቴ ቃልህን ተናገረ። |
172 My tongue shall speak of thy word: for all thy commandments are righteousness. |
173 ትእዛዛትህን መርጫለሁና እጅህ የሚያድነኝ ይሁን። |
173 Let thine hand help me; for I have chosen thy precepts. |
174 አቤቱ፥ ማዳንህን ናፈቅሁ ሕግህም ተድላዬ ነው። |
174 I have longed for thy salvation, O Lord; and thy law is my delight. |
175 ነፍሴ ትኑርልኝ ታመሰግንህማለች፥ ፍርድህም ይርዳኝ። |
175 Let my soul live, and it shall praise thee; and let thy judgments help me. |
176 እንደ ጠፉ በግ ተቅበዘበዝሁ ትእዛዛትህን አልረሳሁምና ባሪያህን ፈልገው። |
176 I have gone astray like a lost sheep; seek thy servant; for I do not forget thy commandments. |
መዝሙረ ዳዊት 119 Verse 89-176 |
Ps 119 Verse 89-176 |