መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #45
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 45 |
Ps 45 |
1 ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ፥ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሓፊ ብርዕ ነው። |
1 My heart is inditing a good matter: I speak of the things which I have made touching the king: my tongue is the pen of a ready writer. |
2 ውበትህ ከሰው ልጆች ይልቅ ያምራል ሞገስ በከንፈሮችህ ፈሰሰ ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባረከህ። |
2 Thou art fairer than the children of men: grace is poured into thy lips: therefore God hath blessed thee for ever. |
3 ኃያል ሆይ፥ በቍንጅናህና በውበትህ ሰይፍህን በወገብህ ታጠቅ። |
3 Gird thy sword upon thy thigh, O most mighty, with thy glory and thy majesty. |
4 ስለ ቅንነትና ስለ የዋህነት ስለ ጽድቅም አቅና ተከናወን ንገሥም ቀኝህም በክብር ይመራሃል። |
4 And in thy majesty ride prosperously because of truth and meekness and righteousness; and thy right hand shall teach thee terrible things. |
5 ኃያል ሆይ፥ ፍላጻዎችህ የተሳሉ ናቸው፥ እነርሱም በንጉሥ ጠላቶች ልብ ውስጥ ይገባሉ፥ አሕዛብም በበታችህ ይወድቃሉ። |
5 Thine arrows are sharp in the heart of the king’s enemies; whereby the people fall under thee. |
6 አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘላለም ነው የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው። |
6 Thy throne, O God, is for ever and ever: the sceptre of thy kingdom is a right sceptre. |
7 ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክ የደስታ ዘይትን ቀባህ። |
7 Thou lovest righteousness, and hatest wickedness: therefore God, thy God, hath anointed thee with the oil of gladness above thy fellows. |
8 በልብሶችህ ሁሉ ከርቤና ሽቱ ዝባድም አሉ ከዝሆን ጥርሶች አዳራሽ ደስ ያሰኙሃል። |
8 All thy garments smell of myrrh, and aloes, and cassia, out of the ivory palaces, whereby they have made thee glad. |
9 የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች። |
9 Kings’ daughters were among thy honourable women: upon thy right hand did stand the queen in gold of Ophir. |
10 ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ |
10 Hearken, O daughter, and consider, and incline thine ear; forget also thine own people, and thy father’s house; |
11 ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። |
11 So shall the king greatly desire thy beauty: for he is thy Lord; and worship thou him. |
12 የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ። |
12 And the daughter of Tyre shall be there with a gift; even the rich among the people shall intreat thy favour. |
13 ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብርዋ ነው ልብስዋ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው። |
13 The king’s daughter is all glorious within: her clothing is of wrought gold. |
14 በኋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ፥ ባልንጀሮችዋንም ወደ አንተ ያቀርባሉ |
14 She shall be brought unto the king in raiment of needlework: the virgins her companions that follow her shall be brought unto thee. |
15 በደስታና በሐሴት ይወስዱአቸዋል፥ ወደ ንጉሥ እልፍኝም ያስገቡአቸዋል። |
15 With gladness and rejoicing shall they be brought: they shall enter into the king’s palace. |
16 በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ። |
16 Instead of thy fathers shall be thy children, whom thou mayest make princes in all the earth. |
17 ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ ስለዚህ ለዓለምና ለዘላለም አሕዛብ ይገዙልሃል። |
17 I will make thy name to be remembered in all generations: therefore shall the people praise thee for ever and ever. |