መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #52
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 52

Psalm 52

1 ኃያል ሆይ፥ በክፋት ለምን ትጓደዳለህ? ሁልጊዜስ በመተላለፍ?

1 Why boastest thou thyself in mischief, O mighty man? the goodness of God endureth continually.

2 አንደበትህ ኃጢአትን ያስባል እንደ ተሳለ ምላጭ ሽንገላን አደረግህ።

2 Thy tongue deviseth mischiefs; like a sharp razor, working deceitfully.

3 ከመልካም ይልቅ ክፋትን፥ ጽድቅንም ከመናገር ይልቅ ዓመፃን ወደድህ።

3 Thou lovest evil more than good; and lying rather than to speak righteousness. Selah.

4 የሚያጠፉ ቃልን ሁሉ፥ የሽንገላ ምላስን ወደድህ።

4 Thou lovest all devouring words, O thou deceitful tongue.

5 ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ያፈርስሃል ከቤትህም ይነቅልሃል ያፈልስሃልም፥ ሥርህንም ከሕያዋን ምድር።

5 God shall likewise destroy thee for ever, he shall take thee away, and pluck thee out of thy dwelling place, and root thee out of the land of the living. Selah.

6 ጻድቃን አይተው ይፈራሉ በእርሱም ይሥቃሉ እንዲህም ይላሉ።

6 The righteous also shall see, and fear, and shall laugh at him:

7 እግዚአብሔርን ረዳቱ ያላደረገ፥ በባለጠግነቱም ብዛት የታመነ፥ በከንቱ ነገርም የበረታ ያ ሰው እነሆ።

7 Lo, this is the man that made not God his strength; but trusted in the abundance of his riches, and strengthened himself in his wickedness.

8 እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ ለዓለምና ለዘላለም በእግዚአብሔር ምሕረት ታመንሁ።

8 But I am like a green olive tree in the house of God: I trust in the mercy of God for ever and ever.

9 አድርገህልኛልና ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፥ በቅዱሳንህም ዘንድ መልካም ነውና ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ።

9 I will praise thee for ever, because thou hast done it: and I will wait on thy name; for it is good before thy saints.