ኦሪት ዘጸአት Orit ZeTseAt
Exodus / Shemot #2
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘጸአት 2

Exodus 2

1 ከሌዊ ወገንም አንድ ሰው ሄዶ የሌዊን ልጅ አገባ።

1 And there went a man of the house of Levi, and took to wife a daughter of Levi.

2 ሴቲቱም ፀነሰች፥ ወንድ ልጅም ወለደች መልካምም እንደሆነ ባየች ጊዜ ሦስት ወር ሸሸገችው።

2 And the woman conceived, and bare a son: and when she saw him that he was a goodly child, she hid him three months.

3 ደግሞም ልትሸሽገው ባልቻለች ጊዜ፥ የደንገል ሣጥን ለእርሱ ወስዳ ዝፍትና ቅጥራን ለቀለቀችው ሕፃኑንም አኖረችበት፥ በወንዝም ዳር ባለ በቄጠማ ውስጥ አስቀመጠችው።

3 And when she could not longer hide him, she took for him an ark of bulrushes, and daubed it with slime and with pitch, and put the child therein; and she laid it in the flags by the river’s brink.

4 እኅቱም የሚደረግበትን ታውቅ ዘንድ በሩቅ ቆማ ትጎበኘው ነበር።

4 And his sister stood afar off, to wit what would be done to him.

5 የፈርዖንም ልጅ ልትታጠብ ወደ ወንዝ ወረደች ደንገጥሮችዋም በወንዝ ዳር ይሄዱ ነበር ሣጥኑንም በቄጠማ ውስጥ አየች፥ ደንገጥርዋንም ልካ አስመጣችው።

5 And the daughter of Pharaoh came down to wash herself at the river; and her maidens walked along by the river’s side; and when she saw the ark among the flags, she sent her maid to fetch it.

6 በከፈተችውም ጊዜ ሕፃኑን አየች፥ እነሆም ሕፃኑ ያለቅስ ነበር አዘነችለትም። ይህ ከዕብራውያን ልጆች አንድ ነው አለች።

6 And when she had opened it, she saw the child: and, behold, the babe wept. And she had compassion on him, and said, This is one of the Hebrews’ children.

7 እኅቱም ለፈርዖን ልጅ። ሕፃኑን ታጠባልሽ ዘንድ ሄጄ የምታጠባ ሴት ከዕብራውያን ሴቶች ልጥራልሽን? አለቻት።

7 Then said his sister to Pharaoh’s daughter, Shall I go and call to thee a nurse of the Hebrew women, that she may nurse the child for thee?

8 የፈርዖንም ልጅ። ሂጂ አለቻት ብላቴናይቱም ሄዳ የሕፃኑን እናት ጠራች።

8 And Pharaoh’s daughter said to her, Go. And the maid went and called the child’s mother.

9 የፈርዖንም ልጅ። ይህን ሕፃን ወስደሽ አጥቢልኝ፥ ዋጋሽንም እሰጥሻለሁ አለቻት። ሴቲቱም ሕፃኑን ወስዳ አጠባችው።

9 And Pharaoh’s daughter said unto her, Take this child away, and nurse it for me, and I will give thee thy wages. And the woman took the child, and nursed it.

10 ሕፃኑም አደገ፥ ወደ ፈርዖንም ልጅ ዘንድ አመጣችው፥ ለእርስዋም ልጅ ሆነላት። እኔ ከውኃ አውጥቼዋለሁና ስትልም ስሙን ሙሴ ብላ ጠራችው።

10 And the child grew, and she brought him unto Pharaoh’s daughter, and he became her son. And she called his name Moses: and she said, Because I drew him out of the water.

11 በዚያም ወራት እንዲህ ሆነ ሙሴ ጎበዝ በሆነ ጊዜ ወደ ወንድሞቹ ወጣ፥ የሥራቸውንም መከራ ተመለከተ የግብፅም ሰው የወንድሞቹን የዕብራውያንን ሰው ሲመታ አየ።

11 And it came to pass in those days, when Moses was grown, that he went out unto his brethren, and looked on their burdens: and he spied an Egyptian smiting an Hebrew, one of his brethren.

12 ወዲህና ወዲያም ተመለከተ፥ ማንንም አላየም፥ ግብፃዊውንም ገደለ፥ በአሸዋም ውስጥ ሸሸገው።

12 And he looked this way and that way, and when he saw that there was no man, he slew the Egyptian, and hid him in the sand.

13 በሁለተኛውም ቀን ወጣ፥ ሁለቱም የዕብራውያን ሰዎች ሲጣሉ አየ በዳዩንም። ለምን ባልንጀራህን ትመታዋለህ? አለው።

13 And when he went out the second day, behold, two men of the Hebrews strove together: and he said to him that did the wrong, Wherefore smitest thou thy fellow?

14 ያም። በእኛ ላይ አንተን አለቃ ወይስ ዳኛ ማን አደረገህ? ወይስ ግብፃዊውን እንደ ገደልኸው ልትገድለኝ ትሻለህን? አለው። ሙሴም፦ በእውነት ይህ ነገር ታውቆአል ብሎ ፈራ።

14 And he said, Who made thee a prince and a judge over us? intendest thou to kill me, as thou killedst the Egyptian? And Moses feared, and said, Surely this thing is known.

15 ፈርዖንም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ሙሴን ሊገድለው ፈለገ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ፊት ኰበለለ፥ በምድያምም ምድር ተቀመጠ በውኃም ጕድጓድ አጠገብ ዐረፈ።

15 Now when Pharaoh heard this thing, he sought to slay Moses. But Moses fled from the face of Pharaoh, and dwelt in the land of Midian: and he sat down by a well.

16 ለምድያምም ካህን ሰባት ሴቶች ልጆች ነበሩት እነርሱም መጥተው ውኃ ቀዱ፥ የአባታቸውንም በጎች ሊያጠጡ የውኃውን ገንዳ ሞሉ።

16 Now the priest of Midian had seven daughters: and they came and drew water, and filled the troughs to water their father’s flock.

17 እረኞችም መጥተው ገፉአቸው ሙሴ ግን ተነሥቶ ረዳቸው፥ በጎቻቸውንም አጠጣላቸው።

17 And the shepherds came and drove them away: but Moses stood up and helped them, and watered their flock.

18 ወደ አባታቸው ወደ ራጉኤልም በመጡ ጊዜ። ስለ ምን ዛሬ ፈጥናችሁ መጣችሁ? አላቸው።

18 And when they came to Reuel their father, he said, How is it that ye are come so soon to day?

19 እርሱም፦ አንድ የግብፅ ሰው ከእረኞች እጅ አዳነን፥ ደግሞም ቀዳልን፥ በጎቻችንንም አጠጣ አሉ።

19 And they said, An Egyptian delivered us out of the hand of the shepherds, and also drew water enough for us, and watered the flock.

20 ልጆቹንም። እርሱ ወዴት ነው? ለምንስ ያንን ሰው ተዋችሁት? ጥሩት እንጀራም ይብላ አላቸው።

20 And he said unto his daughters, And where is he? why is it that ye have left the man? call him, that he may eat bread.

21 ሙሴም ከዚያ ሰው ጋር ሊቀመጥ ወደደ ልጁንም ሲፓራን ለሙሴ ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠው።

21 And Moses was content to dwell with the man: and he gave Moses Zipporah his daughter.

22 ወንድ ልጅም ወለደች። በሌላ ምድር መጻተኛ ነኝ ሲል ስሙን ጌርሳም ብሎ ጠራው።

22 And she bare him a son, and he called his name Gershom: for he said, I have been a stranger in a strange land.

23 ከዚያም ከብዙ ቀን በኋላ እንዲህ ሆነ የግብፅ ንጉሥ ሞተ የእስራኤልም ልጆች ከባርነት የተነሣ አለቀሱ፥ ጮኹም፥ ስለ ባርነታቸውም ጩኸታቸው ወደ እግዚአብሔር ወጣ።

23 And it came to pass in process of time, that the king of Egypt died: and the children of Israel sighed by reason of the bondage, and they cried, and their cry came up unto God by reason of the bondage.

24 እግዚአብሔርም የለቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፥ እግዚአብሔርም ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን አሰበ።

24 And God heard their groaning, and God remembered his covenant with Abraham, with Isaac, and with Jacob.

25 እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች አየ፥ እግዚአብሔርም በእነርሱ ያለውን ነገር አወቀ።

25 And God looked upon the children of Israel, and God had respect unto them.