ኦሪት ዘጸአት Orit ZeTseAt
Exodus / Shemot #23
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

 

ኦሪት ዘጸአት 23

Exodus 23

1 ሐሰተኛ ወሬ አትቀበል ሐሰተኛ ምስክርም ትሆን ዘንድ ከኃጢአተኛ ጋር እጅህን አታንሣ።

1 Thou shalt not raise a false report: put not thine hand with the wicked to be an unrighteous witness.

2 ክፉውን ለማድረግ ብዙ ሰዎችን አትከተል ፍርድንም ለማጥመም ከብዙ ሰዎች ጋር ተስማምተህ አትመስክር።

2 Thou shalt not follow a multitude to do evil; neither shalt thou speak in a cause to decline after many to wrest judgment:

3 በፍርድ ነገርም ለድሀው አታድላ።

3 Neither shalt thou countenance a poor man in his cause.

4 የጠላትህን በሬ ወይም አህያውን ጠፍቶ ብታገኘው በፍጹም መልስለት።

4 If thou meet thine enemy’s ox or his ass going astray, thou shalt surely bring it back to him again.

5 የሚጠላህን ሰው አህያ ከሸክሙ በታች ወድቆ ብታየው አትተወው፥ ነገር ግን ከእርሱ ጋር አንሣው።

5 If thou see the ass of him that hateth thee lying under his burden, and wouldest forbear to help him, thou shalt surely help with him.

6 በሚምዋገትበት ጊዜ የድሀህን ፍርድ አታጥምም።

6 Thou shalt not wrest the judgment of thy poor in his cause.

7 ከሐሰት ነገር ራቅ እኔ ኃጢአተኛውን አላጸድቅምና ንጹሕንና ጻድቅን አትግደል።

7 Keep thee far from a false matter; and the innocent and righteous slay thou not: for I will not justify the wicked.

8 ማማለጃን አትቀበል ማማለጃ የዓይናማዎችን ሰዎች ዓይን ያሳውራልና፥ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና።

8 And thou shalt take no gift: for the gift blindeth the wise, and perverteth the words of the righteous.

9 በስደተኛው ግፍ አታድርጉ እናንተ በግብፅ ምድር ስደተኞች ስለ ነበራችሁ የስደተኛ ነፍስ እንዴት እንደ ሆነች አውቃችኋልና።

9 Also thou shalt not oppress a stranger: for ye know the heart of a stranger, seeing ye were strangers in the land of Egypt.

10 ስድስት ዓመት ምድርህን ዝራ፥ ፍሬዋንም አግባ

10 And six years thou shalt sow thy land, and shalt gather in the fruits thereof:

11 በሰባተኛው ዓመት ግን ተዋት አሳርፋትም የሕዝብህም ድሆች ይበሉታል ያስቀሩትንም የሜዳ እንስሳ ይብላው። እንዲሁም በወይንህና በወይራህ አድርግ።

11 But the seventh year thou shalt let it rest and lie still; that the poor of thy people may eat: and what they leave the beasts of the field shall eat. In like manner thou shalt deal with thy vineyard, and with thy oliveyard.

12 ስድስት ቀን ሥራህን ሥራ በሬህና አህያህ ያርፉ ዘንድ ለባሪያህም ልጅ ለመጻተኛውም ዕረፍት ይሆን ዘንድ በሰባተኛው ቀን ዕረፍ።

12 Six days thou shalt do thy work, and on the seventh day thou shalt rest: that thine ox and thine ass may rest, and the son of thy handmaid, and the stranger, may be refreshed.

13 ያልኋችሁንም ነገር ሁሉ ጠብቁ የሌሎችንም አማልክት ስም አትጥሩ፥ ከአፋችሁም አይሰማ።

13 And in all things that I have said unto you be circumspect: and make no mention of the name of other gods, neither let it be heard out of thy mouth.

14 በዓመት ሦስት ጊዜ በዓል ታደርግልኛለህ።

14 Three times thou shalt keep a feast unto me in the year.

15 የቂጣውን በዓል ጠብቅ በአቢብ ወር ከግብፅ ምድር ወጥታችኋልና በዚህ ወር እንዳዘዝሁህ ሰባት ቀን ቂጣ እንጀራ ትበላለህ በፊቴም ባዶ እጃችሁን አትታዩ።

15 Thou shalt keep the feast of unleavened bread: (thou shalt eat unleavened bread seven days, as I commanded thee, in the time appointed of the month Abib; for in it thou camest out from Egypt: and none shall appear before me empty:)

16 በእርሻም የምትዘራትን የፍሬህን በኵራት የመከር በዓል፥ ዓመቱም ሳያልቅ ፍሬህን ከእርሻ ባከማቸህ ጊዜ የመክተቻውን በዓል ጠብቅ።

16 And the feast of harvest, the firstfruits of thy labours, which thou hast sown in the field: and the feast of ingathering, which is in the end of the year, when thou hast gathered in thy labours out of the field.

17 በዓመት ሦስት ጊዜ በአንተ ዘንድ ያለው ወንድ ሁሉ በጌታ በእግዚአብሔር ፊት ይታይ።

17 Three times in the year all thy males shall appear before the Lord God.

18 የመሥዋዕቴን ደም ከቦካ እንጀራ ጋር አትሠዋ የበዓሌም ስብ እስኪነጋ አይደር።

18 Thou shalt not offer the blood of my sacrifice with leavened bread; neither shall the fat of my sacrifice remain until the morning.

19 የተመረጠውን የምድርህን ፍሬ በኵራት ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ቤት አምጣ። ጠቦትን በእናቱ ወተት አትቀቅል።

19 The first of the firstfruits of thy land thou shalt bring into the house of the Lord thy God. Thou shalt not seethe a kid in his mother’s milk.

20 በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።

20 Behold, I send an Angel before thee, to keep thee in the way, and to bring thee into the place which I have prepared.

21 በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።

21 Beware of him, and obey his voice, provoke him not; for he will not pardon your transgressions: for my name is in him.

22 አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፥ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፥ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፥ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ።

22 But if thou shalt indeed obey his voice, and do all that I speak; then I will be an enemy unto thine enemies, and an adversary unto thine adversaries.

23 መልአኬ በፊትህ ይሄዳልና፥ ወደ አሞራውያንም ወደ ኬጢያውያንም ወደ ፌርዛውያንም ወደ ከነዓናውያንም ወደ ኤዊያውያንም ወደ ኢያቡሳውያንም ያገባሃል እኔም አጠፋቸዋለሁ።

23 For mine Angel shall go before thee, and bring thee in unto the Amorites, and the Hittites, and the Perizzites, and the Canaanites, the Hivites, and the Jebusites: and I will cut them off.

24 ለአማልክቶቻቸው አትስገድ፥ አታምልካቸውም እንደ ሥራቸውም አትሥራ ነገር ግን ፈጽመህ አፍርሳቸው፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብራቸው።

24 Thou shalt not bow down to their gods, nor serve them, nor do after their works: but thou shalt utterly overthrow them, and quite break down their images.

25 አምላካችሁንም እግዚአብሔርን ታመልኩታላችሁ፥ እርሱም እህልህንና ውኃህን ይባርካል በሽታንም ከመካከልህ አርቃለሁ።

25 And ye shall serve the Lord your God, and he shall bless thy bread, and thy water; and I will take sickness away from the midst of thee.

26 በምድርህም መካን ወይም የምትጨነግፍ አትሆንም የዘመንህን ቍጥር እሞላለሁ።

26 There shall nothing cast their young, nor be barren, in thy land: the number of thy days I will fulfil.

27 መፈራቴንም በፊትህ እሰድዳለሁ፥ የምትሄድበትንም ሕዝብ ሁሉ አስደነግጣቸዋለሁ፥ ጠላቶችህንም ሁሉ በፊትህ ጀርባቸውን እንዲያዞሩ አደርጋለሁ።

27 I will send my fear before thee, and will destroy all the people to whom thou shalt come, and I will make all thine enemies turn their backs unto thee.

28 በፊትህም ተርብ እሰድዳለሁ፥ ኤዊያዊውንም ከነዓናዊውንም ኬጢያዊውንም ከፊትህ አባርራለሁ።

28 And I will send hornets before thee, which shall drive out the Hivite, the Canaanite, and the Hittite, from before thee.

29 ምድር ባድማ እንዳትሆን፥ የምድር አራዊትም እንዳይበዙብህ፥ በአንድ ዓመት ከፊታችሁ አላባርራቸውም።

29 I will not drive them out from before thee in one year; lest the land become desolate, and the beast of the field multiply against thee.

30 ነገር ግን እስክትበዛ ምድርንም እስክትወርስ ድረስ በጥቂት በጥቂት አባርራቸዋለሁ።

30 By little and little I will drive them out from before thee, until thou be increased, and inherit the land.

31 ድንበርህንም ከኤርትራ ባሕር እስከ ፍልስጥኤም ባሕር፥ ከምድረ በዳም እስከ ወንዙ ድረስ አደርጋለሁ በምድር የሚኖሩትን በእጅህ እጥላለሁና ከፊትህም ታባርራቸዋለሁ።

31 And I will set thy bounds from the Red sea even unto the sea of the Philistines, and from the desert unto the river: for I will deliver the inhabitants of the land into your hand; and thou shalt drive them out before thee.

32 ከእነርሱና ከአማልክቶቻቸው ጋር ቃል ኪዳን አታድርግ።

32 Thou shalt make no covenant with them, nor with their gods.

33 አማልክቶቻቸውንም ብታመልክ ወጥመድ ይሆኑብሃልና እኔን እንድትበድል እንዳያደርጉህ በአገርህ አይቀመጡ።

33 They shall not dwell in thy land, lest they make thee sin against me: for if thou serve their gods, it will surely be a snare unto thee.