ኦሪት ዘሌዋውያን Orit ZeLaeWaWiYan
Leviticus / Vayikra #2
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

 

ኦሪት ዘሌዋውያን 2

Leviticus 2

1 ማናቸውም ሰው የእህል ቍርባን ለእግዚአብሔር ሲያቀርብ ቍርባኑ ከመልካም ዱቄት ይሁን ዘይትም ያፈስስበታል፥ ዕጣንም ይጨምርበታል

1 And when any will offer a meat offering unto the Lord, his offering shall be of fine flour; and he shall pour oil upon it, and put frankincense thereon:

2 ወደ አሮንም ልጆች ወደ ካህናቱ ያመጣዋል ከመልካም ዱቄቱና ከዘይቱም አንድ እፍኝ ሙሉና ዕጣኑን ሁሉ ወስዶ ካህኑ የእሳት ቍርባን ለእግዚአብሔር ጣፋጭ ሽታ እንዲሆን ለመታሰቢያ በመሠዊያው ላይ ያቃጥለዋል።

2 And he shall bring it to Aaron’s sons the priests: and he shall take thereout his handful of the flour thereof, and of the oil thereof, with all the frankincense thereof; and the priest shall burn the memorial of it upon the altar, to be an offering made by fire, of a sweet savour unto the Lord:

3 ከእህሉም ቍርባን የተረፈው ለአሮንና ለልጆቹ ይሆናል ይህም ለእግዚአብሔር የሚሆን የእሳት ቍርባን ቅዱሰ ቅዱሳን ነው።

3 And the remnant of the meat offering shall be Aaron’s and his sons’: it is a thing most holy of the offerings of the Lord made by fire.

4 በእቶን የተጋገረውን የእህል ቍርባን ስታቀርብ በዘይት የተለወሰ የመልካም ዱቄት የቂጣ እንጐቻ ወይም በዘይት የተቀባ ስስ ቂጣ ይሁን።

4 And if thou bring an oblation of a meat offering baken in the oven, it shall be unleavened cakes of fine flour mingled with oil, or unleavened wafers anointed with oil.

5 ቍርባንህም በምጣድ የተጋገረ የእህል ቍርባን ቢሆን፥ በዘይት የተለወሰ የመልካም ዱቄት ቂጣ ይሁን።

5 And if thy oblation be a meat offering baken in a pan, it shall be of fine flour unleavened, mingled with oil.

6 ቈርሰህም ዘይት ታፈስስበታለህ የእህል ቍርባን ነው።

6 Thou shalt part it in pieces, and pour oil thereon: it is a meat offering.

7 ቍርባንህም በመቀቀያ የበሰለ የእህል ቍርባን ቢሆን፥ ዘይት የገባበት ከመልካም ዱቄት የተደረገ ይሁን።

7 And if thy oblation be a meat offering baken in the fryingpan, it shall be made of fine flour with oil.

8 ከዚህም የተደረገውን የእህል ቍርባን ወደ እግዚአብሔር ታመጣለህ ለካህኑም ይሰጣል፥ እርሱም ወደ መሠዊያው ያቀርበዋል።

8 And thou shalt bring the meat offering that is made of these things unto the Lord: and when it is presented unto the priest, he shall bring it unto the altar.

9 ካህኑም ከእህሉ ቍርባን መታሰቢያውን አንሥቶ የእሳት ቍርባን ለእግዚአብሔር ጣፋጭ ሽታ እንዲሆን በመሠዊያው ላይ ያቃጥለዋል።

9 And the priest shall take from the meat offering a memorial thereof, and shall burn it upon the altar: it is an offering made by fire, of a sweet savour unto the Lord.

10 ከእህሉም ቍርባን የተረፈው ለአሮንና ለልጆቹ ይሆናል ይህም ለእግዚአብሔር የሚሆን የእሳት ቍርባን ቅዱሰ ቅዱሳን ነው።

10 And that which is left of the meat offering shall be Aaron’s and his sons’: it is a thing most holy of the offerings of the Lord made by fire.

11 እርሾ ያለበት ነገር ማርም ለእግዚአብሔር የእሳት ቍርባን ይሆን ዘንድ አታቀርቡምና ለእግዚአብሔር የምታቀርቡት የእህል ቍርባን ሁሉ እርሾ አይሁንበት።

11 No meat offering, which ye shall bring unto the Lord, shall be made with leaven: for ye shall burn no leaven, nor any honey, in any offering of the Lord made by fire.

12 እነዚህንም የበኵራት ቍርባን አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር ታቀርባላችሁ እንደ ጣፋጭ ሽታ ግን በመሠዊያው ላይ አይቃጠሉም።

12 As for the oblation of the firstfruits, ye shall offer them unto the Lord: but they shall not be burnt on the altar for a sweet savour.

13 የምታቀርበውን የእህል ቍርባን ሁሉ በጨው ታጣፍጠዋለህ የአምላክህንም ቃል ኪዳን ጨው ከእህል ቍርባንህ አታጐድልም በቍርባንህ ሁሉ ላይ ጨው ታቀርባለህ።

13 And every oblation of thy meat offering shalt thou season with salt; neither shalt thou suffer the salt of the covenant of thy God to be lacking from thy meat offering: with all thine offerings thou shalt offer salt.

14 ከበኵራትም የእህል ቍርባን ለእግዚአብሔር ብታቀርብ ስለዚህ ቍርባን በእሳት የተጠበሰና የተፈተገ የእህል እሸት ታቀርባለህ።

14 And if thou offer a meat offering of thy firstfruits unto the Lord, thou shalt offer for the meat offering of thy firstfruits green ears of corn dried by the fire, even corn beaten out of full ears.

15 ዘይትም ታፈስስበታለህ፥ ዕጣንም ትጨምርበታለህ የእህል ቍርባን ነው።

15 And thou shalt put oil upon it, and lay frankincense thereon: it is a meat offering.

16 ካህኑም ከተፈተገው እህል ከዘይቱም ወስዶ ከዕጣኑ ሁሉ ጋር መታሰቢያውን ያቃጥላል ይህ ለእግዚአብሔር የእሳት ቍርባን ነው።

16 And the priest shall burn the memorial of it, part of the beaten corn thereof, and part of the oil thereof, with all the frankincense thereof: it is an offering made by fire unto the Lord.