መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon | Mishlei Shlomo #2
In Amharic and English
መጽሐፈ ምሳሌ 2 |
Proverbs 2 |
1 ልጄ ሆይ፥ ቃሌን ብትቀበል፥ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት፥ |
1 My son, if thou wilt receive my words, and hide my commandments with thee; |
2 ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፥ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ። |
2 So that thou incline thine ear unto wisdom, and apply thine heart to understanding; |
3 ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት፥ ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሣ፥ |
3 Yea, if thou criest after knowledge, and liftest up thy voice for understanding; |
4 እርስዋንም እንደ ብር ብትፈላልጋት፥ እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት |
4 If thou seekest her as silver, and searchest for her as for hid treasures; |
5 የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፥ የአምላክንም እውቀት ታገኛለህ። |
5 Then shalt thou understand the fear of the Lord, and find the knowledge of God. |
6 እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና ከአፉም እውቀትና ማስተዋል ይወጣሉ |
6 For the Lord giveth wisdom: out of his mouth cometh knowledge and understanding. |
7 እርሱ ለቅኖች ደኅንነትን ያከማቻል ያለ ነውር ለሚሄዱትም ጋሻ ነው |
7 He layeth up sound wisdom for the righteous: he is a buckler to them that walk uprightly. |
8 የፍርድን ጎዳና ይጠብቃል የቅዱሳኑንም መንገድ ያጸናል። |
8 He keepeth the paths of judgment, and preserveth the way of his saints. |
9 የዚያን ጊዜ ጽድቅንና ፍርድን ቅንነትንና መልካም መንገድን ሁሉ ታስተውላለህ። |
9 Then shalt thou understand righteousness, and judgment, and equity; yea, every good path. |
10 ጥበብ ወደ ልብህ ትገባለችና፥ እውቀትም ነፍስህን ደስ ታሰኛለችና |
10 When wisdom entereth into thine heart, and knowledge is pleasant unto thy soul; |
11 ጥንቃቄ ይጠብቅሃል፥ ማስተዋልም ይጋርድሃል፥ |
11 Discretion shall preserve thee, understanding shall keep thee: |
12 ከክፉ መንገድ አንተን ለማዳን፥ ጠማማ ነገርን ከሚናገሩም ሰዎች |
12 To deliver thee from the way of the evil man, from the man that speaketh froward things; |
13 እነርሱም በጨለማ መንገድ ይሄዱ ዘንድ የቀናውን ጎዳና የሚተው፥ |
13 Who leave the paths of uprightness, to walk in the ways of darkness; |
14 ክፉ በመሥራት ደስ የሚላቸው በጠማማነትም ደስታን የሚያደርጉ፥ |
14 Who rejoice to do evil, and delight in the frowardness of the wicked; |
15 መንገዳቸውን የሚጠመዝዙ አካሄዳቸውንም የሚያጣምሙ ናቸው |
15 Whose ways are crooked, and they froward in their paths: |
16 ከጋለሞታ ሴት አንተን ለመታደግ፥ ቃልዋን ከምታለዝብ ከሌላዪቱም ሴት |
16 To deliver thee from the strange woman, even from the stranger which flattereth with her words; |
17 የሕፃንነት ወዳጅዋን የምትተው የአምላክዋንም ቃል ኪዳን የምትረሳ |
17 Which forsaketh the guide of her youth, and forgetteth the covenant of her God. |
18 ቤትዋ ወደ ሞት ያዘነበለ ነው፥ አካሄድዋም ወደ ሙታን ጥላ። |
18 For her house inclineth unto death, and her paths unto the dead. |
19 ወደ እርስዋ የሚገቡ ሁሉ አይመለሱም፥ የሕይወትንም ጎዳና አያገኙም |
19 None that go unto her return again, neither take they hold of the paths of life. |
20 አንተም በደጋግ ሰዎች መንገድ እንድትሄድ የጻድቃንንም ጎዳና እንድትጠብቅ። |
20 That thou mayest walk in the way of good men, and keep the paths of the righteous. |
21 ቅኖች በምድር ላይ ይቀመጣሉና፥ ፍጹማንም በእርስዋ ይኖራሉና |
21 For the upright shall dwell in the land, and the perfect shall remain in it. |
22 ኃጥኣን ግን ከምድር ይጠፋሉ፥ ዓመፀኞችም ከእርስዋ ይነጠቃሉ። |
22 But the wicked shall be cut off from the earth, and the transgressors shall be rooted out of it. |