መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #139
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 139

Psalm 139

1 አቤቱ፥ መረመርኸኝ፥ አወቅኸኝም።

1 O Lord, thou hast searched me, and known me.

2 አንተ መቀመጤንና መነሣቴን አወቅህ አሳቤን ሁሉ ከሩቅ አስተዋልህ።

2 Thou knowest my downsitting and mine uprising, thou understandest my thought afar off.

3 ፍለጋዬንና ዕረፍቴን አንተ መረመርህ መንገዶቼን ሁሉ ቀድመህ አወቅህ፥

3 Thou compassest my path and my lying down, and art acquainted with all my ways.

4 የዓመፃ ቃል በአንደበቴ እንደሌለ።

4 For there is not a word in my tongue, but, lo, O Lord, thou knowest it altogether.

5 አቤቱ፥ አንተ እነሆ የቀድሞውንና የኋላውን አወቅህ አንተ ፈጠርኸኝ፥ እጅህንም በላዬ አደረግህ።

5 Thou hast beset me behind and before, and laid thine hand upon me.

6 እውቀትህ ከእኔ ይልቅ ተደነቀች በረታች፥ ወደ እርስዋም ለመድረስ አልችልም።

6 Such knowledge is too wonderful for me; it is high, I cannot attain unto it.

7 ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?

7 Whither shall I go from thy spirit? or whither shall I flee from thy presence?

8 ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ አለህ። ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ።

8 If I ascend up into heaven, thou art there: if I make my bed in hell, behold, thou art there.

9 እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥

9 If I take the wings of the morning, and dwell in the uttermost parts of the sea;

10 በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች።

10 Even there shall thy hand lead me, and thy right hand shall hold me.

11 በውኑ ጨለማ ትሸፍነኛለች ብል፥ ሌሊት በዙሪያዬ ብርሃን ትሆናለች

11 If I say, Surely the darkness shall cover me; even the night shall be light about me.

12 ጨለማ በአንተ ዘንድ አይጨልምምና፥ ሌሊትም እንደ ቀን ታበራለችና እንደ ጨለማዋ እንዲሁ ብርሃንዋ ነው።

12 Yea, the darkness hideth not from thee; but the night shineth as the day: the darkness and the light are both alike to thee.

13 አቤቱ፥ አንተ ኵላሊቴን ፈጥረሃልና፥ በእናቴም ሆድ ሰውረኸኛል።

13 For thou hast possessed my reins: thou hast covered me in my mother’s womb.

14 ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች።

14 I will praise thee; for I am fearfully and wonderfully made: marvellous are thy works; and that my soul knoweth right well.

15 እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፥ አካሌም በምድር ታች በተሠራ ጊዜ አጥንቶቼ ከአንተ አልተሰወሩም።

15 My substance was not hid from thee, when I was made in secret, and curiously wrought in the lowest parts of the earth.

16 ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ።

16 Thine eyes did see my substance, yet being unperfect; and in thy book all my members were written, which in continuance were fashioned, when as yet there was none of them.

17 አቤቱ፥ አሳቦችህ በእኔ ዘንድ እንደ ምን እጅግ የተከበሩ ናቸው! ቍጥራቸውም እንደ ምን በዛ!

17 How precious also are thy thoughts unto me, O God! how great is the sum of them!

18 ብቈጥራቸው ከአሸዋ ይልቅ ይበዛሉ ተነሣሁም፥ እኔም ገና ከአንተ ጋር ነኝ።

18 If I should count them, they are more in number than the sand: when I awake, I am still with thee.

19 አቤቱ፥ አንተ ኃጢአተኞችን የምትገድል ከሆንህስ፥ የደም ሰዎች ሆይ፥ ከእኔ ፈቀቅ በሉ።

19 Surely thou wilt slay the wicked, O God: depart from me therefore, ye bloody men.

20 በክፋት ይናገሩብሃልና ጠላቶችህም በከንቱ ያምፁብሃል።

20 For they speak against thee wickedly, and thine enemies take thy name in vain.

21 አቤቱ፥ የሚጠሉህን እኔ የጠላሁ አይደለሁምን? ስለ ጠላቶችህም አልተሰቀቅሁምን?

21 Do not I hate them, O Lord, that hate thee? and am not I grieved with those that rise up against thee?

22 ፍጹም ጥል ጠላኋቸው፥ ጠላቶችም ሆኑኝ።

22 I hate them with perfect hatred: I count them mine enemies.

23 አቤቱ፥ መርምረኝ ልቤንም እወቅ ፍተነኝ መንገዴንም እወቅ

23 Search me, O God, and know my heart: try me, and know my thoughts:

24 በደልንም በእኔ ውስጥ ብታገኝ እይ የዘላለምንም መንገድ ምራኝ።

24 And see if there be any wicked way in me, and lead me in the way everlasting.