መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #142
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 142

Psalm 142

1 በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ለመንሁ።

1 I cried unto the Lord with my voice; with my voice unto the Lord did I make my supplication.

2 ልመናዬን በፊቱ አፈስሳለሁ መከራዬንም በፊቴ እናገራለሁ።

2 I poured out my complaint before him; I shewed before him my trouble.

3 ነፍሴ በውስጤ ባለቀች ጊዜ መንገዴን አወቅሁ በምሄድባት በዚያች መንገድ ወጥመድን ሰወሩብኝ።

3 When my spirit was overwhelmed within me, then thou knewest my path. In the way wherein I walked have they privily laid a snare for me.

4 ወደ ቀኝ ተመለከትሁ አየሁም፥ የሚያውቀኝም አጣሁ መሸሸጊያም የለኝም፥ ስለ ነፍሴም የሚመራመር የለም።

4 I looked on my right hand, and beheld, but there was no man that would know me: refuge failed me; no man cared for my soul.

5 አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ። አንተ ተስፋዬ ነህ፥ በሕያዋንም ምድር አንተ እድል ፈንታዬ ነህ አልሁ።

5 I cried unto thee, O Lord: I said, Thou art my refuge and my portion in the land of the living.

6 እጅግ ተቸግሬአለሁና ወደ ልመናዬ አድምጥ በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።

6 Attend unto my cry; for I am brought very low: deliver me from my persecutors; for they are stronger than I.

7 አቤቱ፥ ስምህን አመሰግን ዘንድ ነፍሴን ከወህኒ አውጣት ዋጋዬን እስክትሰጠኝ ድረስ ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ።

7 Bring my soul out of prison, that I may praise thy name: the righteous shall compass me about; for thou shalt deal bountifully with me.