መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #141
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 141 |
Psalm 141 |
1 አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ ስማኝ ወደ አንተ ስጮኽም የልመናዬን ቃል አድምጥ። |
1 Lord, I cry unto thee: make haste unto me; give ear unto my voice, when I cry unto thee. |
2 ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጅ መንሣቴም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን። |
2 Let my prayer be set forth before thee as incense; and the lifting up of my hands as the evening sacrifice. |
3 አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ። |
3 Set a watch, O Lord, before my mouth; keep the door of my lips. |
4 ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው፥ ዓመፃን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋር ለኃጢአት ምክንያት እንዳልሰጥ ከምርጦቻቸውም ጋር አልተባበር። |
4 Incline not my heart to any evil thing, to practise wicked works with men that work iniquity: and let me not eat of their dainties. |
5 ጻድቅ በምሕረት ይገሥጸኝ፥ ይዝለፈኝም፥ የኃጢአተኛ ዘይት ግን ራሴን አይቅባ ጸሎቴ ገና በክፋታቸው ላይ ነውና። |
5 Let the righteous smite me; it shall be a kindness: and let him reprove me; it shall be an excellent oil, which shall not break my head: for yet my prayer also shall be in their calamities. |
6 ኃያላኖቻቸው በዓለት አጠገብ ተጣሉ ጣፋጭ ናትና ቃሌን ይሰማሉ። |
6 When their judges are overthrown in stony places, they shall hear my words; for they are sweet. |
7 በምድር ላይ እንደ ተሰነጠቀ እንደ መሬት ጓል፥ እንዲሁ አጥንቶቻችን በሲኦል ተበተኑ። |
7 Our bones are scattered at the grave’s mouth, as when one cutteth and cleaveth wood upon the earth. |
8 አቤቱ ጌታ፥ ዓይኖቼ ወደ አንተ ናቸውና በአንተ ታመንሁ፥ ነፍሴን አታውጣት። |
8 But mine eyes are unto thee, O God the Lord: in thee is my trust; leave not my soul destitute. |
9 ከሰወሩብኝ ወጥመድ፥ ዓመፅንም ከሚያደርጉ ሰዎች ዕንቅፋት ጠብቀኝ። |
9 Keep me from the snares which they have laid for me, and the gins of the workers of iniquity. |
10 እኔ ብቻዬን እስካልፍ ድረስ ኃጢአተኞች በወጥመዳቸው ይውደቁ። |
10 Let the wicked fall into their own nets, whilst that I withal escape. |