መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #143
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 143 |
Psalm 143 |
1 አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ በእውነትህ ልመናዬን አድምጥ፥ በጽድቅህም መልስልኝ። |
1 Hear my prayer, O Lord, give ear to my supplications: in thy faithfulness answer me, and in thy righteousness. |
2 ሕያው ሁሉ በፊትህ ጻድቅ አይደለምና ከባሪያህ ጋር ወደ ፍርድ አትግባ። |
2 And enter not into judgment with thy servant: for in thy sight shall no man living be justified. |
3 ጠላትህ ነፍሴን አሳድዶአታል፥ ሕይወቴንም በምድር ውስጥ አጐስቍሎአታል ቀድሞ እንደ ሞተ ሰው በጨለማ አኑሮኛል። |
3 For the enemy hath persecuted my soul; he hath smitten my life down to the ground; he hath made me to dwell in darkness, as those that have been long dead. |
4 ነፍሴ በውስጤ አለቀችብኝ፥ ልቤም በውስጤ ደነገጠብኝ። |
4 Therefore is my spirit overwhelmed within me; my heart within me is desolate. |
5 የቀድሞውን ዘመን አሰብሁ፥ ሥራህንም ሁሉ አሰላሰልሁ የእጅህንም ሥራ ተመለከትሁ። |
5 I remember the days of old; I meditate on all thy works; I muse on the work of thy hands. |
6 እጆቼን ወደ አንተ ዘረጋሁ ነፍሴም እንደ ምድረ በዳ አንተን ተጠማች። |
6 I stretch forth my hands unto thee: my soul thirsteth after thee, as a thirsty land. Selah. |
7 አቤቱ፥ ፈጥነህ ስማኝ ነፍሴ አልቃለች ፊትህን ከኔ አትመልስ፥ ወደ ጕድጓድም እንደሚወርዱ አልሁን። |
7 Hear me speedily, O Lord: my spirit faileth: hide not thy face from me, lest I be like unto them that go down into the pit. |
8 አንተን ታምኛለሁና በማለዳ ምሕረትህን አሰማኝ አቤቱ፥ ነፍሴን ወደ አንተ አንሥቻለሁና የምሄድበትን መንገድ አስታውቀኝ። |
8 Cause me to hear thy lovingkindness in the morning; for in thee do I trust: cause me to know the way wherein I should walk; for I lift up my soul unto thee. |
9 አቤቱ፥ ወደ አንተ ተማፅኛለሁና ከጠላቶቼ አድነኝ። |
9 Deliver me, O Lord, from mine enemies: I flee unto thee to hide me. |
10 አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ለማድረግ አስተምረኝ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ ምድር ይምራኝ። |
10 Teach me to do thy will; for thou art my God: thy spirit is good; lead me into the land of uprightness. |
11 አቤቱ፥ ስለ ስምህ ሕያው አድርገኝ በጽድቅህም ነፍሴን ከመከራዋ አውጣት። |
11 Quicken me, O Lord, for thy name’s sake: for thy righteousness’ sake bring my soul out of trouble. |
12 በምሕረትህ ጠላቶቼን ደምስሳቸው፥ እኔ ባሪያህ ነኝና ነፍሴን የሚያስጨንቁአትን ሁሉ አጥፋቸው። |
12 And of thy mercy cut off mine enemies, and destroy all them that afflict my soul: for I am thy servant. |