መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #37
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 37

Ps 37

1 በክፉዎች ላይ አትቅና፥ ዓመፃንም በሚያደርጉ ላይ አትቅና

1 Fret not thyself because of evildoers, neither be thou envious against the workers of iniquity.

2 እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፥ እንደ ለመለመ ቅጠልም ይረግፋሉና።

2 For they shall soon be cut down like the grass, and wither as the green herb.

3 በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ።

3 Trust in the Lord, and do good; so shalt thou dwell in the land, and verily thou shalt be fed.

4 በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል።

4 Delight thyself also in the Lord; and he shall give thee the desires of thine heart.

5 መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።

5 Commit thy way unto the Lord; trust also in him; and he shall bring it to pass.

6 ጽድቅህን እንደ ብርሃን፦ ፍርድህንም እንደ ቀትር ያመጣል።

6 And he shall bring forth thy righteousness as the light, and thy judgment as the noonday.

7 ለእግዚአብሔር ተገዛ ተስፋም አድርገው። መንገድም በቀናችለትና ጥመትን በሚያደርግ ሰው አትቅና።

7 Rest in the Lord, and wait patiently for him: fret not thyself because of him who prospereth in his way, because of the man who bringeth wicked devices to pass.

8 ከቁጣ ራቅ መዓትንም ተው እንዳትበድል አትቅና።

8 Cease from anger, and forsake wrath: fret not thyself in any wise to do evil.

9 ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉና እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ።

9 For evildoers shall be cut off: but those that wait upon the Lord, they shall inherit the earth.

10 ገና ጥቂት፥ ኃጢአተኛም አይኖርም ትፈልገዋለህ ቦታውንም አታገኝም።

10 For yet a little while, and the wicked shall not be: yea, thou shalt diligently consider his place, and it shall not be.

11 ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፥ በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል።

11 But the meek shall inherit the earth; and shall delight themselves in the abundance of peace.

12 ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለካከተዋል፥ ጥርሱንም በእርሱ ላይ ያንገጫግጫል።

12 The wicked plotteth against the just, and gnasheth upon him with his teeth.

13 እግዚአብሔር ይሥቅበታል፥ ቀኑ እንደሚደርስ አይቶአልና።

13 The Lord shall laugh at him: for he seeth that his day is coming.

14 ኃጢአተኞች ሰይፋቸውን መዘዙ፥ ቀስታቸውንም ገተሩ ድሀውንና ችግረኛውን ይጥሉ ዘንድ ልበ ቅኖችንም ይወጉ ዘንድ

14 The wicked have drawn out the sword, and have bent their bow, to cast down the poor and needy, and to slay such as be of upright conversation.

15 ሰይፋቸው ወደ ልባቸው ይግባ፥ ቀስታቸውም ይሰበር።

15 Their sword shall enter into their own heart, and their bows shall be broken.

16 ለጻድቅ ያለው ጥቂት ከብዙ ከኃጢአተኞች ሀብት ይበልጣል።

16 A little that a righteous man hath is better than the riches of many wicked.

17 የኃጥአን ክንድ ትሰበራለችና እግዚአብሔር ግን ጻድቃንን ይደግፋቸዋል።

17 For the arms of the wicked shall be broken: but the Lord upholdeth the righteous.

18 የንጹሓንን መንገድ እግዚአብሔር ያውቃል፥ ርስታቸውም ለዘላለም ነው

18 The Lord knoweth the days of the upright: and their inheritance shall be for ever.

19 በክፉ ዘመንም አያፍሩም በራብ ዘመንም ይጠግባሉ።

19 They shall not be ashamed in the evil time: and in the days of famine they shall be satisfied.

20 ኅጥአን ግን ይጠፋሉ፥ የእግዚአብሔር ጠላቶች በከበሩና ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ እንደ ጢስ ይጠፋሉ።

20 But the wicked shall perish, and the enemies of the Lord shall be as the fat of lambs: they shall consume; into smoke shall they consume away.

21 ኃጢአተኛ ይበደራል አይከፍልምም ጻድቅ ግን ይራራል ይሰጣልም።

21 The wicked borroweth, and payeth not again: but the righteous sheweth mercy, and giveth.

22 እርሱን የሚባርኩት ምድርን ይወርሳሉና የሚረግሙት ግን ይጠፋሉ።

22 For such as be blessed of him shall inherit the earth; and they that be cursed of him shall be cut off.

23 የሰው አካሄድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይጸናል፥ መንገዱንም ይወድዳል።

23 The steps of a good man are ordered by the Lord: and he delighteth in his way.

24 ቢወድቅም ለድንጋፄ አይጣልም፥ እግዚአብሔር እጁን ይዞ ይደግፈዋልና።

24 Though he fall, he shall not be utterly cast down: for the Lord upholdeth him with his hand.

25 ጐለመስሁ አረጀሁም ጻድቅ ሲጣል፥ ዘሩም እህል ሲለምን አላየሁም።

25 I have been young, and now am old; yet have I not seen the righteous forsaken, nor his seed begging bread.

26 ሁልጊዜ ይራራል ያበድርማል፥ ዘሩም በበረከት ይኖራል።

26 He is ever merciful, and lendeth; and his seed is blessed.

27 ከክፉ ሽሽ፥ መልካምንም አድርግ ለዘላለምም ትኖራለህ።

27 Depart from evil, and do good; and dwell for evermore.

28 እግዚአብሔር ፍርዱን ይወድዳልና፥ ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል ለንጹሓንም ይበቀልላቸዋል የኅጥኣን ዘር ግን ይጠፋል።

28 For the Lord loveth judgment, and forsaketh not his saints; they are preserved for ever: but the seed of the wicked shall be cut off.

29 ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፥ በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ።

29 The righteous shall inherit the land, and dwell therein for ever.

30 የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል፥ አንደበቱም ፍርድን ይናገራል።

30 The mouth of the righteous speaketh wisdom, and his tongue talketh of judgment.

31 የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው፥ በእርምጃውም አይሰናከልም።

31 The law of his God is in his heart; none of his steps shall slide.

32 ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለከተዋል፥ ሊገድለውም ይወድዳል።

32 The wicked watcheth the righteous, and seeketh to slay him.

33 እግዚአብሔር ግን በእጁ አይተወውም፥ በተፋረደውም ጊዜ አያሸንፈውም።

33 The Lord will not leave him in his hand, nor condemn him when he is judged.

34 እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፥ መንገዱንም ጠብቅ፥ ምድርንም ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል ኃጢአተኞችም ሲጠፉ ታያለህ።

34 Wait on the Lord, and keep his way, and he shall exalt thee to inherit the land: when the wicked are cut off, thou shalt see it.

35 ኃጥአን ከፍ ከፍ ብሎ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ለምልሞ አየሁት።

35 I have seen the wicked in great power, and spreading himself like a green bay tree.

36 ብመለስ ግን አጣሁት ፈለግሁት ቦታውንም አላገኘሁም።

36 Yet he passed away, and, lo, he was not: yea, I sought him, but he could not be found.

37 ቅንነትን ጠብቅ፥ ጽድቅንም እይ ለሰላም ሰው ቅሬታ አለውና።

37 Mark the perfect man, and behold the upright: for the end of that man is peace.

38 በደለኞች በአንድነት ይጠፋሉ። የኃጢአተኞች ቅሬታ ይጠፋል።

38 But the transgressors shall be destroyed together: the end of the wicked shall be cut off.

39 የጻድቃን መድኃኒታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው በመከራቸውም ጊዜ መጠጊያቸው እርሱ ነው።

39 But the salvation of the righteous is of the Lord: he is their strength in the time of trouble.

40 እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፥ ያድናቸዋልም፥ ከኃጢአተኞችም እጅ ያወጣቸዋል፥ ያድናቸዋል፥ በእርሱ ታምነዋልና።

40 And the Lord shall help them, and deliver them: he shall deliver them from the wicked, and save them, because they trust in him.