መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #6
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 6

Ps 6

1 አቤቱ፥ በቍጣህ አትቅሠፈኝ፥ በመዓትህም አትገሥጸኝ።

1 O Lord, rebuke me not in thine anger, neither chasten me in thy hot displeasure.

2 ድውይ ነኝና አቤቱ፥ ማረኝ አጥንቶቼ ታውከዋልና ፈውሰኝ።

2 Have mercy upon me, O Lord; for I am weak: O Lord, heal me; for my bones are vexed.

3 ነፍሴም እጅግ ታወከች አንተም አቤቱ፥ እስከ መቼ ድረስ ነው?

3 My soul is also sore vexed: but thou, O Lord, how long?

4 አቤቱ፥ ተመለስ ነፍሴንም አድናት፥ ስለ ቸርነትህም አድነኝ።

4 Return, O Lord, deliver my soul: oh save me for thy mercies’ sake.

5 በሞት የሚያስብህ የለምና፥ በሲኦልም የሚያመሰግንህ ማን ነው?

5 For in death there is no remembrance of thee: in the grave who shall give thee thanks?

6 በጭንቀቴ ደክሜያለሁ ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፥ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ።

6 I am weary with my groaning; all the night make I my bed to swim; I water my couch with my tears.

7 ዓይኔ ከቍጡ ዕንባ የተነሣ ታወከች ከጠላቶቼ ሁሉ የተነሣ አረጀሁ።

7 Mine eye is consumed because of grief; it waxeth old because of all mine enemies.

8 ዓመፃን የምታደርጉ ሁሉ፥ ከእኔ ራቁ፥ እግዚአብሔር የልቅሶዬን ቃል ሰምቶአልና።

8 Depart from me, all ye workers of iniquity; for the Lord hath heard the voice of my weeping.

9 እግዚአብሔር ልመናዬን ሰማኝ እግዚአብሔር ጸሎቴን ተቀበለ።

9 The Lord hath heard my supplication; the Lord will receive my prayer.

10 ጠላቶቼ ሁሉ ይፈሩ እጅግም ይጐስቍሉ ወደ ኋላቸው ይመለሱ፥ በፍጥነትም ይፈሩ።

10 Let all mine enemies be ashamed and sore vexed: let them return and be ashamed suddenly.