መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #5
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 5

Ps 5

1 አቤቱ፥ ቃሌን አድምጥ፥ ጩኸቴንም አስተውል

1 Give ear to my words, O Lord, consider my meditation.

2 የልመናዬን ቃል አድምጥ፥ ንጉሤና አምላኬ ሆይ፥ አቤቱ፥ ወደ አንተ እጸልያለሁና።

2 Hearken unto the voice of my cry, my King, and my God: for unto thee will I pray.

3 በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፥ በማለዳ በፊትህ እቆማለሁ፥ እጠብቃለሁም።

3 My voice shalt thou hear in the morning, O Lord; in the morning will I direct my prayer unto thee, and will look up.

4 አንተ በደልን የማትወድድ አምላክ ነህና ክፉ ከአንተ ጋር አያድርም።

4 For thou art not a God that hath pleasure in wickedness: neither shall evil dwell with thee.

5 በከንቱ የሚመኩ በዓይኖችህ ፊት አይኖሩም ክፉ አድራጊዎችን ሁሉ ጠላህ።

5 The foolish shall not stand in thy sight: thou hatest all workers of iniquity.

6 ሐሰትን የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ ደም አፍሳሹንና ሸንጋዩን ሰው እግዚአብሔር ይጸየፋል።

6 Thou shalt destroy them that speak leasing: the Lord will abhor the bloody and deceitful man.

7 እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ አንተን በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ።

7 But as for me, I will come into thy house in the multitude of thy mercy: and in thy fear will I worship toward thy holy temple.

8 አቤቱ፥ ስለ ጠላቶቼ በጽድቅህ ምራኝ መንገዴን በፊትህ አቅና።

8 Lead me, O Lord, in thy righteousness because of mine enemies; make thy way straight before my face.

9 በአፋቸው እውነት የለምና፥ ልባቸውም ከንቱ ነው ጕሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው በምላሳቸው ይሸነግላሉ።

9 For there is no faithfulness in their mouth; their inward part is very wickedness; their throat is an open sepulchre; they flatter with their tongue.

10 አቤቱ፥ ፍረድባቸው፥ በምክራቸውም ይውደቁ ስለ ክፋታቸውም ብዛት አሳድዳቸው፥ እነርሱ ዐምፀውብሃልና።

10 Destroy thou them, O God; let them fall by their own counsels; cast them out in the multitude of their transgressions; for they have rebelled against thee.

11 በአንተ የሚታመኑት ሁሉ ግን ደስ ይላቸዋል ለዘላለሙ ደስ ይላቸዋል፥ እነርሱንም ትጠብቃለህ ስምህንም የሚወድዱ ሁሉ በአንተ ይመካሉ።

11 But let all those that put their trust in thee rejoice: let them ever shout for joy, because thou defendest them: let them also that love thy name be joyful in thee.

12 አንተ ጻድቁን ትባርከዋለህና አቤቱ፥ እንደ ጋሻ በሞገስ ከለልኸን።

12 For thou, Lord, wilt bless the righteous; with favour wilt thou compass him as with a shield.