መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #63
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 63

Psalm 63

1 አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።

1 O God, thou art my God; early will I seek thee: my soul thirsteth for thee, my flesh longeth for thee in a dry and thirsty land, where no water is;

2 ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ።

2 To see thy power and thy glory, so as I have seen thee in the sanctuary.

3 ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

3 Because thy lovingkindness is better than life, my lips shall praise thee.

4 እንዲህ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፥ በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።

4 Thus will I bless thee while I live: I will lift up my hands in thy name.

5 ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ።

5 My soul shall be satisfied as with marrow and fatness; and my mouth shall praise thee with joyful lips:

6 በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ

6 When I remember thee upon my bed, and meditate on thee in the night watches.

7 ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና።

7 Because thou hast been my help, therefore in the shadow of thy wings will I rejoice.

8 ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች፥ እኔንም ቀኝህ ተቀበለችኝ።

8 My soul followeth hard after thee: thy right hand upholdeth me.

9 እነርሱ ግን ነፍሴን ለከንቱ ፈለጓት ወደ ምድር ጥልቅ ይገባሉ።

9 But those that seek my soul, to destroy it, shall go into the lower parts of the earth.

10 ለሰይፍ እጅ አልፈው ይሰጣሉ፥ የቀበሮም እድል ፈንታ ይሆናሉ።

10 They shall fall by the sword: they shall be a portion for foxes.

11 ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል በእርሱ የሚምል ሁሉ ይከብራል፥ ሐሰትን የሚናገር አፍ ይዘጋልና።

11 But the king shall rejoice in God; every one that sweareth by him shall glory: but the mouth of them that speak lies shall be stopped.