መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #61
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 61

Psalm 61

1 አምላክ ሆይ፥ ልመናዬን ስማ፥ ጸሎቴንም አድምጥ።

1 Hear my cry, O God; attend unto my prayer.

2 ልቤ ተስፋ በቈረጠ ጊዜ ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጮኻለሁ በድንጋይ ላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ።

2 From the end of the earth will I cry unto thee, when my heart is overwhelmed: lead me to the rock that is higher than I.

3 ጽኑ ግንብ በጠላት ፊት ተስፋዬም ሆነኸኛልና መራኸኝ።

3 For thou hast been a shelter for me, and a strong tower from the enemy.

4 በድንኳንህ ለዘላለም እኖራለሁ በክንፎችህም ጥላ እጋረዳለሁ

4 I will abide in thy tabernacle for ever: I will trust in the covert of thy wings. Selah.

5 አቤቱ፥ አንተ ስእለቴን ሰምተሃልና ስምህንም ለሚፈሩ ርስትህን ሰጠሃቸው።

5 For thou, O God, hast heard my vows: thou hast given me the heritage of those that fear thy name.

6 ለንጉሥ ከቀን በላይ ቀን ትጨምራለህ፥ ዓመታቱም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሆናሉ።

6 Thou wilt prolong the king’s life: and his years as many generations.

7 በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ይኖራል ይጠብቁት ዘንድ ምሕረትንና እውነትን አዘጋጅለት።

7 He shall abide before God for ever: O prepare mercy and truth, which may preserve him.

8 እንዲሁ ለስምህ ለዘላለም እዘምራለሁ ስእለቴን ሁልጊዜ እፈጽም ዘንድ።

8 So will I sing praise unto thy name for ever, that I may daily perform my vows.