መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #68
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 68 |
Psalm 68 |
1 እግዚአብሔር ይነሣ፥ ጠላቶቹም ይበተኑ፥ የሚጠሉትም ከፊቱ ይሽሹ። |
1 Let God arise, let his enemies be scattered: let them also that hate him flee before him. |
2 ጢስ እንደሚበንን እንዲሁ ይብነኑ ሰም በእሳት ፊት እንደሚቀልጥ፥ እንዲሁ ኅጥኣን ከእግዚአብሔር ፊት ይጥፉ። |
2 As smoke is driven away, so drive them away: as wax melteth before the fire, so let the wicked perish at the presence of God. |
3 ጻድቃንም ደስ ይበላቸው፥ በእግዚአብሔርም ፊት ሐሤት ያድርጉ፥ በደስታም ደስ ይበላቸው። |
3 But let the righteous be glad; let them rejoice before God: yea, let them exceedingly rejoice. |
4 ለእግዚአብሔር ተቀኙ ለስሙም ዘምሩ ወደ ምድረ በዳ ለወጣም መንገድ አድርጉ ስሙ እግዚአብሔር ነው፥ በፊቱም ደስ ይበላችሁ በፊቱም ይደነግጣሉ። |
4 Sing unto God, sing praises to his name: extol him that rideth upon the heavens by his name Jah, and rejoice before him. |
5 እግዚአብሔር በቅዱስ ቦታው ለድሀ አደጎች አባት፥ ለባልቴቶችም ዳኛ ነው። |
5 A father of the fatherless, and a judge of the widows, is God in his holy habitation. |
6 እግዚአብሔር ብቸኞችን በቤት ያሳድራቸዋል፥ እስረኞችንም በኃይሉ ያወጣቸዋል ዓመፀኞች ግን በምድረ በዳ ይኖራሉ። |
6 God setteth the solitary in families: he bringeth out those which are bound with chains: but the rebellious dwell in a dry land. |
7 አቤቱ፥ በሕዝብም ፊት በወጣህ ጊዜ፥ በምድረ በዳም ባለፍህ ጊዜ፥ ምድር ተናወጠች፥ |
7 O God, when thou wentest forth before thy people, when thou didst march through the wilderness; Selah: |
8 ከሲና አምላክ ፊት፥ ከእስራኤል አምላክ ፊት ሰማያትም አንጠበጠቡ። |
8 The earth shook, the heavens also dropped at the presence of God: even Sinai itself was moved at the presence of God, the God of Israel. |
9 አቤቱ፥ የሞገስን ዝናብ ለርስትህ አዘነብህ፥ በደከመም ጊዜ አንተ አጸናኸው። |
9 Thou, O God, didst send a plentiful rain, whereby thou didst confirm thine inheritance, when it was weary. |
10 እንስሶችህ በውስጡ አደሩ አቤቱ፥ በቸርነትህ ለድሆች አዘጋጀህ። |
10 Thy congregation hath dwelt therein: thou, O God, hast prepared of thy goodness for the poor. |
11 እግዚአብሔር ቃሉን ሰጠ የሚያወሩት ብዙ ሠራዊት ናቸው። |
11 The Lord gave the word: great was the company of those that published it. |
12 የሠራዊት ነገሥታት ፈጥነው ይሸሻሉ በቤትም የምትኖር ምርኮን ተካፈለች። |
12 Kings of armies did flee apace: and she that tarried at home divided the spoil. |
13 በርስቶች መካከል ብታድሩ፥ ከብር እንደ ተሠሩ እንደ ርግብ ክንፎች፥ በቅጠልያ ወርቅም እንደ ተለበጡ ላባዎችዋ ትሆናላችሁ። |
13 Though ye have lien among the pots, yet shall ye be as the wings of a dove covered with silver, and her feathers with yellow gold. |
14 ሰማያዊ ንጉሥ በላይዋ ባዘዘ ጊዜ፥ በሰልሞን ላይ በረዶ ዘነበ። |
14 When the Almighty scattered kings in it, it was white as snow in Salmon. |
15 የእግዚአብሔር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው የጸና ተራራና የለመለመ ተራራ ነው። |
15 The hill of God is as the hill of Bashan; an high hill as the hill of Bashan. |
16 የጸኑ ተራራዎች ለምን ይነሣሉ? እግዚአብሔር ይህን ተራራ ያድርበት ዘንድ ወደደው በእውነት እግዚአብሔር ለዘላለም ያድርበታል። |
16 Why leap ye, ye high hills? this is the hill which God desireth to dwell in; yea, the Lord will dwell in it for ever. |
17 የእግዚአብሔር ሰረገላዎች የብዙ ብዙ ሺህ ናቸው ጌታ በመቅደሱ በሲና በመካከላቸው ነው። |
17 The chariots of God are twenty thousand, even thousands of angels: the Lord is among them, as in Sinai, in the holy place. |
18 ወደ ላይ ዓረግህ፥ ምርኮን ማረክህ፥ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ፥ ደግሞም ለዓመፀኞች በዚያ ያድሩ ዘንድ። |
18 Thou hast ascended on high, thou hast led captivity captive: thou hast received gifts for men; yea, for the rebellious also, that the Lord God might dwell among them. |
19 እግዚአብሔር አምላክ ቡሩክ ነው እግዚአብሔር በየዕለቱ ቡሩክ ነው የመድኃኒታችን አምላክ ይረዳናል። |
19 Blessed be the Lord, who daily loadeth us with benefits, even the God of our salvation. Selah. |
20 አምላካችንስ የደኅንነት አምላክ ነው ከሞት መውጣትም ከእግዚአብሔር ነው። |
20 He that is our God is the God of salvation; and unto God the Lord belong the issues from death. |
21 ነገር ግን እግዚአብሔር የጠላቶቹን ራስ፥ በኃጢአት የሚሄድንም የጠጕሩን አናት ይቀጠቅጣል። |
21 But God shall wound the head of his enemies, and the hairy scalp of such an one as goeth on still in his trespasses. |
22 እግዚአብሔር እንዲህ አለ፦ ከባሳን አመጣቸዋለሁ፥ ከባሕርም ጥልቅ እመልሳቸዋለሁ፥ |
22 The Lord said, I will bring again from Bashan, I will bring my people again from the depths of the sea: |
23 እግሮችህ በደም ይረገጡ ዘንድ፥ የውሾችህ ምላስ በጠላቶች ላይ ይሆን ዘንድ። |
23 That thy foot may be dipped in the blood of thine enemies, and the tongue of thy dogs in the same. |
24 የአምላኬ የንጉሥ መንገድ በመቅደሱ፥ አቤቱ፥ መንገድህ ተገለጠ። |
24 They have seen thy goings, O God; even the goings of my God, my King, in the sanctuary. |
25 አለቆች ቀደሙ፥ መዘምራንም ተከተሉ ከበሮን በሚመቱ በቈነጃጅት መካከል። |
25 The singers went before, the players on instruments followed after; among them were the damsels playing with timbrels. |
26 እግዚአብሔርን በጉባኤ፥ ጌታችንንም በእስራኤል ምንጭ አመስግኑት። |
26 Bless ye God in the congregations, even the Lord, from the fountain of Israel. |
27 ወጣቱ ብንያም በጕልበቱ በዚያ አለ፥ ገዦቻቸው የይሁዳ አለቆች የዛብሎን አለቆችና የንፍታሌምም አለቆች። |
27 There is little Benjamin with their ruler, the princes of Judah and their council, the princes of Zebulun, and the princes of Naphtali. |
28 አቤቱ፥ ኃይልህን እዘዝ አቤቱ፥ ይህንም ለእኛ የሠራኸውን አጽናው። |
28 Thy God hath commanded thy strength: strengthen, O God, that which thou hast wrought for us. |
29 በኢየሩሳሌም ስላለው መቅደስህ ነገሥታት እጅ መንሻን ለአንተ ያመጣሉ። |
29 Because of thy temple at Jerusalem shall kings bring presents unto thee. |
30 በሸምበቆ ውስጥ ያሉትን አራዊት፥ በአሕዛብ ውስጥ ያሉትን የበሬዎችንና የወይፈኖችን ጉባኤ ገሥጽ፥ እንደ ብር የተፈተኑት አሕዛብ እንዳይዘጉ ሰልፍን የሚወድዱትን አሕዛብን በትናቸው። |
30 Rebuke the company of spearmen, the multitude of the bulls, with the calves of the people, till every one submit himself with pieces of silver: scatter thou the people that delight in war. |
31 መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። |
31 Princes shall come out of Egypt; Ethiopia shall soon stretch out her hands unto God. |
32 የምድር ነገሥታት፥ ለእግዚአብሔር ተቀኙ፥ ለጌታም ዘምሩ። |
32 Sing unto God, ye kingdoms of the earth; O sing praises unto the Lord; Selah: |
33 በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል። |
33 To him that rideth upon the heavens of heavens, which were of old; lo, he doth send out his voice, and that a mighty voice. |
34 ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ ግርማው በእስራኤል ላይ፥ ኃይሉም በደመናት ላይ ነው። |
34 Ascribe ye strength unto God: his excellency is over Israel, and his strength is in the clouds. |
35 እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል እግዚአብሔርም ይመስገን። |
35 O God, thou art terrible out of thy holy places: the God of Israel is he that giveth strength and power unto his people. Blessed be God. |