መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #88
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 88

Psalm 88

1 አቤቱ፥ የመድኃኒቴ አምላክ፥ በቀንና በሌሊት በፊትህ ጮኽሁ

1 O Lord God of my salvation, I have cried day and night before thee:

2 ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትግባ፥ ጆሮህንም ወደ ጩኸቴ አዘንብል

2 Let my prayer come before thee: incline thine ear unto my cry;

3 ነፍሴ መከራን ጠግባለችና፥ ሕይወቴም ወደ ሲኦል ቀርባለችና።

3 For my soul is full of troubles: and my life draweth nigh unto the grave.

4 ወደ ጓድጓድ ከሚወርዱ ጋር ተቈጠርሁ፥ ረዳትም እንደሌለው ሰው ሆንሁ።

4 I am counted with them that go down into the pit: I am as a man that hath no strength:

5 ለዘላለም እንደማታስባቸው፥ እንደ ተገደሉና በመቃብር ውስጥ እንደ ተጣሉ፥ በሙታን ውስጥ እንዳሉ የተጣልሁ ሆንሁ እነርሱም ከእጅህ ተለዩ።

5 Free among the dead, like the slain that lie in the grave, whom thou rememberest no more: and they are cut off from thy hand.

6 በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ፥ በታችኛው ጕድጓድ አስቀመጥኸኝ።

6 Thou hast laid me in the lowest pit, in darkness, in the deeps.

7 በእኔ ላይ ቍጣህ ጸና፥ መቅሠፍትህን ሁሉ በእኔ ላይ አመጣህ።

7 Thy wrath lieth hard upon me, and thou hast afflicted me with all thy waves. Selah.

8 የሚያውቁኝን ከእኔ አራቅህ በእነርሱ ዘንድ ርኵስ አደረግኸኝ ያዙኝ፥ መውጫም የለኝም።

8 Thou hast put away mine acquaintance far from me; thou hast made me an abomination unto them: I am shut up, and I cannot come forth.

9 ዓይኖቼም በመከራ ፈዘዙ አቤቱ፥ ሁልጊዜ ወደ አንተ ጮኽሁ፥ እጆቼንም ወደ አንተ ዘረጋሁ፥

9 Mine eye mourneth by reason of affliction: Lord, I have called daily upon thee, I have stretched out my hands unto thee.

10 በውኑ ለሙታን ተኣምራት ታደርጋለህን? የሞቱትስ ተነሥተው ያመሰግኑሃልን?

10 Wilt thou shew wonders to the dead? shall the dead arise and praise thee? Selah.

11 በመቃብርስ ውስጥ ቸርነትህን፥ እውነትህንስ በጥፋት ስፍራ ይናገራሉን?

11 Shall thy lovingkindness be declared in the grave? or thy faithfulness in destruction?

12 ተአምራትህ በጨለማ፥ ጽድቅህንም በመርሳት ምድር ትታወቃለችን?

12 Shall thy wonders be known in the dark? and thy righteousness in the land of forgetfulness?

13 አቤቱ፥ እኔ ግን ወደ አንተ ጮኽሁ በጥዋት ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትደርሳለች።

13 But unto thee have I cried, O Lord; and in the morning shall my prayer prevent thee.

14 አቤቱ፥ ነፍሴን ለምን ትጥላለህ? ፊትህንስ ከእኔ ለምን ትሰውራለህ?

14 Lord, why castest thou off my soul? why hidest thou thy face from me?

15 እኔ ከታናሽነቴ ችግረኛ ለሞትም የቀረብሁ ነኝ ከፍ ከፍ ካልሁ በኋላ ግን ተዋረድሁ ተናቅሁም።

15 I am afflicted and ready to die from my youth up: while I suffer thy terrors I am distracted.

16 መቅሠፍትህ በላዬ አለፈ፥ ግርማህም አስደነገጠኝ።

16 Thy fierce wrath goeth over me; thy terrors have cut me off.

17 ሁልጊዜ እንደ ውኃ ከበቡኝ፥ በአንድነትም ያዙኝ።

17 They came round about me daily like water; they compassed me about together.

18 ወዳጄንና ባልንጀራዬን ዘመዶቼንም ከመከራ የተነሣ ከእኔ አራቅህ።

18 Lover and friend hast thou put far from me, and mine acquaintance into darkness.