መጽሐፈ ምሳሌ | MeTsiHaFe MiSaLae
Proverbs of Solomon
| Mishlei Shlomo #22
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መጽሐፈ ምሳሌ 22

Proverbs 22

1 መልካም ስም ከብዙ ባለጠግነት ይሻላል፥ መልካምም ሞገስ ከብርና ከወርቅ ይበልጣል።

1 A good name is rather to be chosen than great riches, and loving favour rather than silver and gold.

2 ባለጠና ድሀ ተገናኙ እግዚአብሔር የሁላቸው ፈጣሪ ነው።

2 The rich and poor meet together: the Lord is the maker of them all.

3 ብልህ ሰው ክፉን አይቶ ይሸሸጋል አላዋቂዎች ግን አልፈው ይጐዳሉ።

3 A prudent man foreseeth the evil, and hideth himself: but the simple pass on, and are punished.

4 ትሕትናና እግዚአብሔርን መፍራት ባለጠግነት ክብር ሕይወትም ነው።

4 By humility and the fear of the Lord are riches, and honour, and life.

5 እሾህና ወጥመድ በጠማማ ሰው መንገድ ናቸው ነፍሱን ግን የሚጠብቅ ከእነርሱ ይርቃል።

5 Thorns and snares are in the way of the froward: he that doth keep his soul shall be far from them.

6 ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።

6 Train up a child in the way he should go: and when he is old, he will not depart from it.

7 ባለጠጋ ድሆችን ይገዛል፥ ተበዳሪም የአበዳሪ ባሪያ ነው።

7 The rich ruleth over the poor, and the borrower is servant to the lender.

8 ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ የቍጣውም በትር ይጠፋል።

8 He that soweth iniquity shall reap vanity: and the rod of his anger shall fail.

9 ርኅሩህ የተባረከ ይሆናል፥ ከእንጀራው ለድሀ ሰጥቶአልና።

9 He that hath a bountiful eye shall be blessed; for he giveth of his bread to the poor.

10 ፌዘኛን ብታወጣ ክርክር ይወጣል፥ ጠብና ስድብም ያልቃል።

10 Cast out the scorner, and contention shall go out; yea, strife and reproach shall cease.

11 የልብን ንጽሕና የሚወድድና ሞገስ በከንፈሩ ያለች፥ ንጉሥ ወዳጁ ይሆናል።

11 He that loveth pureness of heart, for the grace of his lips the king shall be his friend.

12 የእግዚአብሔር ዓይኖች እውቀትን ይጠብቃሉ እርሱ ግን የወስላታውን ቃል ይገለብጣል።

12 The eyes of the Lord preserve knowledge, and he overthroweth the words of the transgressor.

13 ታካች ሰው። አንበሳ በሜዳ ነው በመንገዱ ላይ እሞታለሁ ይላል።

13 The slothful man saith, There is a lion without, I shall be slain in the streets.

14 የጋለሞታ ሴት አፍ የጠለቀ ጕድጓድ ነው እግዚአብሔር የተቈጣው በእርስዋ ይወድቃል።

14 The mouth of strange women is a deep pit: he that is abhorred of the Lord shall fall therein.

15 ስንፍና በሕፃን ልብ ታስሮአል የተግሣጽ በትር ግን ከእርሱ ያርቃታል።

15 Foolishness is bound in the heart of a child; but the rod of correction shall drive it far from him.

16 ለራሱ ጥቅም ለመጨመር ሲል ድሀን የሚጐዳ፥ ለባለጠጋም የሚሰጥ፥ እርሱ ወደ ድህነት ይወድቃል።

16 He that oppresseth the poor to increase his riches, and he that giveth to the rich, shall surely come to want.

17 ጆሮህን አዘንብለህ የጠቢባንን ቃላት ስማ፥ ልብህንም ወደ እውቀቴ አድርግ

17 Bow down thine ear, and hear the words of the wise, and apply thine heart unto my knowledge.

18 እነርሱን በውስጥህ ብትጠብቅ፥ በከንፈሮችህም ላይ የተዘጋጁ ቢሆኑ፥ የተወደደ ነገር ይሆንልሃልና።

18 For it is a pleasant thing if thou keep them within thee; they shall withal be fitted in thy lips.

19 እምነትህ በእግዚአብሔር ይሆን ዘንድ ለአንተ ዛሬ እነሆ አስታወቅሁህ።

19 That thy trust may be in the Lord, I have made known to thee this day, even to thee.

20-21 የእውነትን ቃል እርግጥነት አስታውቅህ ዘንድ፥ ለሚጠይቅህም እውነትን ቃል መመለስ ይቻልህ ዘንድ፥ በምክርና በእውቀት የከበረን ነገር አልጻፍሁልህምን?

20 Have not I written to thee excellent things in counsels and knowledge,
21 That I might make thee know the certainty of the words of truth; that thou mightest answer the words of truth to them that send unto thee?

22 ድሀን በግድ አትበለው ድሀ ነውና ችግረኛውንም በበር አትግፋው

22 Rob not the poor, because he is poor: neither oppress the afflicted in the gate:

23 እግዚአብሔር የእነርሱን ፍርድ ይፋረድላቸዋልና፥ የቀሙአቸውንም ሰዎች ሕይወት ይቀማልና።

23 For the Lord will plead their cause, and spoil the soul of those that spoiled them.

24 ከቍጡ ሰው ጋር ባልንጀራ አትሁን፥ ከወፈፍተኛም ጋት አትሂድ፥

24 Make no friendship with an angry man; and with a furious man thou shalt not go:

25 መንገዱን እንዳትማር ለነፍስህም ወጥመድ እንዳታገኝህ።

25 Lest thou learn his ways, and get a snare to thy soul.

26 እጃቸውን አጋና እንደሚማቱ፥ ለባለ ዕዳዎች እንደሚዋሱ አትሁን

26 Be not thou one of them that strike hands, or of them that are sureties for debts.

27 የምትከፍለው ባይኖርህ፥ ምንጣፍህን ከበታችህ ስለ ምን ይወስዳል?

27 If thou hast nothing to pay, why should he take away thy bed from under thee?

28 አባቶችህ የሠሩትን የቀድሞውን የድንበር ምልክት አታፍልስ።

28 Remove not the ancient landmark, which thy fathers have set.

29 በሥራው የቀጠፈ ሰውን አይተሃልን? በነገሥታት ፊት ይቆማል በተዋረዱም ሰዎች ፊት አይቆምም።

29 Seest thou a man diligent in his business? he shall stand before kings; he shall not stand before mean men.