መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #146
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 146

Psalm 146

1 ሃሌ ሉያ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን አመስግኚ።

1 Praise ye the Lord. Praise the Lord, O my soul.

2 በሕይወቴ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለአምላኬ እዘምራለሁ።

2 While I live will I praise the Lord: I will sing praises unto my God while I have any being.

3 ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ።

3 Put not your trust in princes, nor in the son of man, in whom there is no help.

4 ነፍሱ ትወጣለች ወደ መሬቱም ይመለሳል ያን ጊዜ ምክሩ ሁሉ ይጠፋል።

4 His breath goeth forth, he returneth to his earth; in that very day his thoughts perish.

5 የያዕቆብ አምላክ ረዳቱ የሆነ ተስፋውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምስጉን ነው

5 Happy is he that hath the God of Jacob for his help, whose hope is in the Lord his God:

6 እርሱም ሰማይንና ምድርን ባሕርንም፥ በእነርሱ ያለውንም ሁሉ የፈጠረ እውነትን ለዘላለም የሚጠብቅ

6 Which made heaven, and earth, the sea, and all that therein is: which keepeth truth for ever:

7 ለተበደሉት የሚፈርድ፥ ለተራቡ ምግብን የሚሰጥ ነው። እግዚአብሔር የታሰሩትን ይፈታል

7 Which executeth judgment for the oppressed: which giveth food to the hungry. The Lord looseth the prisoners:

8 እግዚአብሔር የወደቁትን ያነሣል እግዚአብሔር ዕውሮችን ጥበበኞች ያደርጋቸዋል እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል

8 The Lord openeth the eyes of the blind: the Lord raiseth them that are bowed down: the Lord loveth the righteous:

9 እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል ድሀ አደጎችንና ባልቴቶችን ይቀበላል የኃጢአተኞችንም መንገድ ያጠፋል።

9 The Lord preserveth the strangers; he relieveth the fatherless and widow: but the way of the wicked he turneth upside down.

10 እግዚአብሔር ለዘላለም ይነግሣል ጽዮን ሆይ፥ አምላክሽ ለልጅ ልጅ ነው። ሃሌ ሉያ።

10 The Lord shall reign for ever, even thy God, O Zion, unto all generations. Praise ye the Lord.