መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #57
In Amharic and English
|
መዝሙረ ዳዊት 57 |
Psalm 57 |
|
1 ማረኝ፥ አቤቱ፥ ማረኝ፥ ነፍሴ አንተን ታምናለችና ጉዳት እስክታልፍ ድረስ በክንፎችህ ጥላ እታመናለሁ። |
1 Be merciful unto me, O God, be merciful unto me: for my soul trusteth in thee: yea, in the shadow of thy wings will I make my refuge, until these calamities be overpast. |
|
2 ወደሚረዳኝ እግዚአብሔር ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ። |
2 I will cry unto God most high; unto God that performeth all things for me. |
|
3 ከሰማይ ልኮ አዳነኝ፥ ለረገጡኝም ውርደትን ሰጣቸው እግዚአብሔር ቸርነቱንና እውነቱን ላከ። |
3 He shall send from heaven, and save me from the reproach of him that would swallow me up. Selah. God shall send forth his mercy and his truth. |
|
4 ነፍሴን ከአንበሶች መካከል አዳናት። ደንግጬ ተኛሁ የሰው ልጆች ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፥ አንደበታቸው የተሳለ ሾተል ነው። |
4 My soul is among lions: and I lie even among them that are set on fire, even the sons of men, whose teeth are spears and arrows, and their tongue a sharp sword. |
|
5 አምላክ ሆይ፥ በሰማያት ላይ ከፍ ከፍ በል ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትሁን። |
5 Be thou exalted, O God, above the heavens; let thy glory be above all the earth. |
|
6 ለእግሮቼ ወጥመድን አዘጋጁ፥ ነፍሴንም አጐበጡአት ጕድጓድ በፊቴ ቈፈሩ፥ በእርሱም ወደቁ። |
6 They have prepared a net for my steps; my soul is bowed down: they have digged a pit before me, into the midst whereof they are fallen themselves. Selah. |
|
7 ልቤ ጨካኝ ነው፥ አቤቱ፥ ልቤ ጨካኝ ነው እቀኛለሁ፥ እዘምራለሁ። |
7 My heart is fixed, O God, my heart is fixed: I will sing and give praise. |
|
8 ክብሬ ይነሣ፥ በገናና መሰንቆም ይነሡ እኔም ማልጄ እነሣለሁ። |
8 Awake up, my glory; awake, psaltery and harp: I myself will awake early. |
|
9 አቤቱ፥ በአሕዛብ ዘንድ አመሰግንሃለሁ፥ በወገኖችም ዘንድ እዘምርልሃለሁ |
9 I will praise thee, O Lord, among the people: I will sing unto thee among the nations. |
|
10 ምሕረትህ እስከ ሰማይ ድረስ ከፍ ብላለችና፥ እውነትህም እስከ ደመናት ድረስ። |
10 For thy mercy is great unto the heavens, and thy truth unto the clouds. |
|
11 አምላክ ሆይ፥ በሰማያት ላይ ከፍ ከፍ በል ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትሁን። |
11 Be thou exalted, O God, above the heavens: let thy glory be above all the earth. |


































































































