መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #8
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 8

Ps 8

1 አቤቱ ጌታችን፥ ስምህ በምድር ሁሉ እጅግ ተመሰገነ፥ ምስጋናህ በሰማዮች ላይ ከፍ ከፍ ብሎአልና።

1 O Lord our Lord, how excellent is thy name in all the earth! who hast set thy glory above the heavens.

2 ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ስለ ጠላትህ፥ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት።

2 Out of the mouth of babes and sucklings hast thou ordained strength because of thine enemies, that thou mightest still the enemy and the avenger.

3 የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፥ ጨረቃንና ከዋክብትን አንተ የሠራሃቸውን፥

3 When I consider thy heavens, the work of thy fingers, the moon and the stars, which thou hast ordained;

4 ታስበው ዘንድ ሰው ምንድር ነው? ትጐበኘውም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድር ነው?

4 What is man, that thou art mindful of him? and the son of man, that thou visitest him?

5 ከመላእክት እጅግ ጥቂት አሳነስኸው በክብርና በምስጋና ዘውድ ከለልኸው።

5 For thou hast made him a little lower than the angels, and hast crowned him with glory and honour.

6 በእጆችህም ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት፥

6 Thou madest him to have dominion over the works of thy hands; thou hast put all things under his feet:

7 በጎችንም ላሞችንም ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፥

7 All sheep and oxen, yea, and the beasts of the field;

8 የሰማይንም ወፎች የባሕርንም ዓሦች፥ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።

8 The fowl of the air, and the fish of the sea, and whatsoever passeth through the paths of the seas.

9 አቤቱ ጌታችን፥ ስምህ በምድር ሁሉ እጅግ ተመሰገነ።

9 O Lord our Lord, how excellent is thy name in all the earth!